Tuesday, May 6, 2014


አባ ዱላ ገመዳ ስለኦሮሚያ ተማሪዎችና ጥያቄዎቻቸው ለቪኦኤ መግለጫ ሰጡ

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አባዱላ ገመዳ “ተቃውሞ ያሰሙ አንዳንድ የኦሮሞ ተማሪዎች በመንግሥት ኃይሎች መገደላቸው ስህተት ነው” አሉ።


አፈ ጉባዔው ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተቃዋሚዎቹ ተገቢ ጥያቄ እንዳነሱ ጠቅሰው ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግም ሕገ-መንግሥታዊ መብት መሆኑን የጠቀሱት አባዱላ ተማሪዎቹ ግን ሠልፍ ለማድረግ መንግሥት የሚጠይቀውን መስፈርት አላሟሉም ብለዋል።

“በተለይም ብዙ ሰዎች በተገደሉበት በአምቦ ከተማ ተማሪዎች ያልሆኑ ያሏቸው ሰልፉን በመቀላቀል ንብረት በማውደማቸው መንግሥት እርምጃ ለመውሰድ ተገድዷል” ብለዋል፡፡

Thursday, May 1, 2014

ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም!!!


ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲንቅናቄ፣ ዘረኛው ወያኔ በኦሮሚያ ሕዝብና ወጣቶች ላይ እያካሄደው ያለውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ፣ እስርና አፈናን በጥብቅ ይቃወማል። ህወሓት፣ ኦህዴድ እና በዚህ ጭፍጨፋ እጃቸው ያለበት ሁሉ ከተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑን ያስገነዝባል።
የአሮሚያ ወጣቶች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም የድሀ ገበሬዎች መፈናቀልን መቃወማቸው ፍትሀዊ ነው። የወያኔ “ማስተር ፕላኖች” የወያኔ የዘረፋ እቅዶች መሆናቸው በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው። ነዋሪዎቹን ያላማከረ፣ ግንባር ቀደም ባለጉዳዮችን ባለቤት ያላደረገ፣ የሕዝብ ይሁንታ ያላገኘ ማስተር ፕላን ተፈፃሚ ማድረግ አይቻልም።
ወያኔ ኦሮሚያን ብቻ ሳይሆን መላዋን ኢትዮጵያ በምስለኔዎቹ አማካይነት እየገዛ የኢትዮጵያን ውድ ልጆች በራሳቸው ጉዳይ ባይተዋር አድርጓቸዋል። ኦህዴድ በወያኔ ቅጥረኛነት የኦሮሚያ ወጣቶችን በማስጨፍጨፍ ላይ ያለ እኩይ የአድርባዮች ስብስብ ነው።  ወጣቶች የተቃወሙት ይህንን ነው።እነዚህ ወጣቶች በአካባቢያቸው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባቸዋል። ድምፃቸው ሊሰማ ይገባል። የሌላው አካባቢም ወጣት የኦሮሚያ ገበሬ መፈናቀል ያገባዋል። ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ በሚደረግ ጉዳይ ሁሉ ያገባናል። በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ወያኔ የራሱን እቅድ እንዲጭንብን አንፈልግም።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ወጣቶች ጥያቄ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ አድርጎ እንዲወስድ ጥሪ ያደርጋል።  በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል የተጀመረው መፈናቀል ዛሬ አዲስ አበባ አጎራባች ከተሞች ደርሷል። በአምቦ ይህንን የተቃወሙ ወጣቶች በግፍ ተጨፍጭፈዋል፤ በሌሎች ቦታዎችም ላይ ግድያውና እስሩ በርትቷል። ወጣቱ  የጥይት እራት ሆኖ እስኪያልቅ መጠበቅ አንችልም፤ ሁሉም ትግሉን ይቀላቀል።
የወያኔ የጥቃት ሰለባ የሆኑት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይን ያነሱ ወጣቶች ብቻ  አይደሉም። በአንድ ወይም በሌላ መንገድ የወያኔን አምባገንነት የተቃወሙ በሙሉ የጥቃቱ ሰላባዎች ናቸው። ለሰልፍ ቅስቀሳ አደረጋችሁ በሚል የታሰሩ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ሰልፉ ተደርጎ  ካለቀ በኋላም አልተፈቱም።  ይህ ሰቆቃ ማብቃት አለበት።
ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

ተጨማሪ መረጃዎች በህገ ወጡ መጅሊስ መፈንቅለ ስልጣን ዙሪያ!


ድምፃችን ይሰማ 


ሐሙስ ሚያዝያ 23/2006

በትናንቱ ሰበር ዜና በህገ ወጡ የፌደራል መጅሊስ ውስጥ የተደረገው መፈንቅለ ስልጣን ፕሬዝዳንቱን እስከማባረር መድረሱን ለማየት ተሞክሯል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን እነሆ!

የውዝግቡ ምንጭ በየካቲት አጋማሽ በድሬዳዋ ከተማ ላይ በተደረገው 11ኛው የመጅሊስ ጠቅላይ ጉባዔ ላይ የተሰጠው የአቋም መግለጫ ሲሆን በአቋም መግለጫው ላይ የተካተቱት አንዳንድ ነጥቦች መጅሊሱ ውስጥ ‹‹ለዘብተኛ›› አቋም የያዘውን ቡድን ለማግለልና ለማባረር ያቀዱ መሆናቸውም ተቃውሞ አስነስቷል፡፡

የአቋም መግለጫው መንስኤ መንግስት ከህዝበ ሙስሊሙ ፍላጎት ውጭ በመስከረም 27/2005 በቀበሌዎች ባካሄደው ህገ ወጥ የመጅሊስ ምርጫ ወደስልጣን ያመጣቸው አካላት ሁሉም በእኩል ደረጃ ጸረ-ሙስሊም አጀንዳውን ሊያስፈጽሙለት ባለመቻላቸው አካሄዱን እየተቃወሙት ያሉትን የአመራር አባላት ለማስወገድ ያለው ፍላጎት ነው፡፡ በአቋም መግለጫው ላይ በተካተቱት ነጥቦች መሰረት በተለይ መጅሊሱ በክልል ደረጃ ባለው ስልጣን የስራ አስፈጻሚ አባላቱን ውክልና ማንሳት እንዲችል መደረጉ (ነጥብ 4) ከመተዳደሪያ ደንቡ ጋር በግልጽ የሚጋጭ ሲሆን ይህም ‹‹እንዲወገዱ የፈለጋቸውን ሰዎች ያለ ህጋዊ ሂደት ማባረር እንዲችል መንገድ ይከፍታል›› የሚል ተቃውሞ እንዲነሳበት አድርጓል፡፡ ይህ ደግሞ በአቋም መግለጫው 1፣ 3፣ 4፣ 5 እና 10ኛ ተራ ቁጥሮች ላይ የተንጸባረቁት ሌሎች ነጥቦች፣ ማለትም አመራሩ ራሱን ከ‹‹አክራሪ››፣ ‹‹ወሐቢያ››፣ ‹‹ኢኽዋን›› እና ‹‹ተክፊር›› ማጥራትና ‹‹ጽንፈኞችን›› ማባረር እንዳለበት ከተቀመጠው ነጥብ ጋር ተዳምሮ መንግጅሊሱ ለሚያስፈጽመው የመንግስት እኩይ አጀንዳ እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ አካላትን የማስወገድ መብት ይሰጠዋል ማለት ነው፡፡ እንግዲህ ይህ ‹‹መጅሊሱ ሁሉንም አስተሳሰቦች አቻችሎ ቢሄድ ነው የሚሻለው›› የሚል አቋም ያራመዱትንና በትናንትናው እለት መፈንቅለ ስልጣን የተደረገባቸውን አባላት ከአክራሪው መፍቅሬ-አህባሽ ቡድን ጋር ካወዛገቡት ነጥቦች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡

ሌላው በአቋም መግለጫው ላይ መካተቱ የውዝግብ ምንጭ ያደረገው ነጥብ ደግሞ ከመንግጅሊሱ ቀጣይ እንቅስቃሴና አህባሽን አስገድዶ የመጫን ሂደት ጋር ተያይዞ የተያዘው አቋም ሲሆን ለዘብተኛው የአመራር ቡድን ‹‹መጅሊሱ ዳግም የህዝበ ሙስሊሙን ተቃውሞ ሊያገረሹ ከሚችሉ አካሄዶች መቆጠብ አለበት›› የሚል አቋም በመጅሊሱ ውስጥ ማራመዱ ጥርስ አስነክሶበታል፡፡ ይህ ቁጥብነት ከፌደራል ጉዳዮች ቀጥተኛ ትእዛዝ ብቻ በመቀበል እየተንቀሳቀሱ ላሉት መፍቅሬ-አህባሽ ቡድኖችም ራስ ምታት ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በመሆኑም በተቋሙ ስም መንግስት ያሻውን እንዳይፈጽም እንቅፋት የሆኑበትን አካላት ሁሉ ካሁን ቀደም ለረጅም ጊዜ በመጅሊሱ ውስጥ ሲያደርገው እንደቆየው ‹‹ውክልና ማንሳት›› የምትባለውን ዘዴ በመጠቀም ‹‹ለዘብተኞቹን›› ከጨዋታ ውጭ አድርጓቸዋል፡፡ በመጅሊሱ ታሪክ በአጋጣሚም ሆነ ባለማወቅ ከመንግስት ቁጥጥር ወይም ፍላጎት ውጭ በመጅሊሱ መዋቅር ውስጥ የገቡ አካላት፣ አልያም በመንግስት ፍላጎት ገብተው ኋላ ላይ ከመንግስት የተለየ አቋም ሲያራምዱ የተገኙ አመራር አባላት ሲወገዱ የነበረው በዚሁ ዘዴ ነበር፡፡ ዛሬም ያንኑ ያረጀ ስልት ራሳቸው በቀበሌ የ‹‹ቅርጫ›› ሂደት መርጠው ባቋቋሙት ህገ ወጥ ካቢኔ ላይ ደግመውታል - ታሪክ ራሱን ይደግማል እንዲሉ!

በጉዳዩ ላይ የህዝበ ሙስሊሙ አቋም ግልጽ ነው፤ ህዝበ ሙስሊሙ መሪዎቹን ራሱ መምረጥ ይፈልጋል! በመጅሊሱ ውስጥ ከህዝብ እውቅናና ፍላጎት ውጭ ጥሩም ሆነ መጥፎ፣ ለዘብተኛም ሆነ ጽንፈኛ መሪዎች መምጣታቸውን ያወግዛል! መረዎቹን መምረጥ ያበት ህዝበ ሙስሊሙ ራሱ ብቻ ነውና!

(ከታች በመፈንቅለ ስልጣኑ የተባረሩት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸኽ ኪያር ሸኽ ሙሀመድ አማን በድሬዳዋው ጉባዔ የጸደቀውን የአቋም መግለጫ ተቃውመው ለተለያዩ የመንግስት አካላት በመጋቢት 26 እና 29/2006 የጻፏቸው ሁለት ደብዳቤዎች እና በድሬዳዋው ጉባዔ የተላለፈውን የአቋም መግለጫ የሰፈረበት የፎቶ አልበም ተያይዟል)

https://www.facebook.com/media/set/?set=a.747502598634432.1073741858.324725940912102&type=3&uploaded=9

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!
ህገ ወጥ መጅሊሱ የሚገኝበትን ሁኔታ አስመልክቶ ፕሬዝዳንቱ ሸኽ ኪያር የጻፉት ደብዳቤ Page 1 of 3

በኦሮሚያ የተጀመረው ተቃውሞ መካረ ስጋት ፈጥሯል

ኦህዴድ የተከፋፈለ አቋም ይዟል፤ ኢህአዴግ ጉልበት መርጧል!!

በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተቃውሞ ድምጽ ለማሰማት በሞከሩና ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ሰልፍ በወጡ ወገኖች ላይ አገዛዙ የ”ከፋ” ነው የተባለ ሃይል መጠቀሙ ተሰማ። ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ታስረዋል። ለተቃውሞ መነሻ በሆነው አዲሱ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ኦህአዴድ ተመሳሳይ አቋም መያዝ አልቻለም። ችግሩን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ያልቻለው ኢህአዴግ ጉልበት መምረጡ አገሪቱ ውስጥ ካለው የተከማቸ ብሶቶች ጋር ተዳምሮ አለመረጋጋቱን ያሰፋዋል የሚል ስጋት አለ።
ከኦሮሚያ ክልል አስተዳደር የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት በአቀራረቡ ቢለያይም ከተለያዩ ሚዲያዎች የሚሰሙት ዜናዎች ሊስተባበሉ የሚችሉ አይደሉም። በታችኛው እርከን የሚገኙትን ጨምሮ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በጥቅሉ፣ ገሃድ አይውጣ እንጂ በመዋቅር ውስጥ ያሉ ሰራተኞችና ካድሬዎች የተቃውሞው ተሳታፊና ደጋፊ መሆናቸውን ክልሉም ሆነ ኢህአዴግ አረጋግጠዋል።
demoየአዲስ አበባ አዲሱ ማስተር ፕላን በዙሪያዋ ያሉትን ስድስት የኦሮሚያን ከተሞችና ስድስት የገጠር ቀበሌዎች የተካተቱበት መሆኑ ያስነሳው ተቃውሞ ቀደም ሲል በክልሉ በምክር ቤት ደረጀ በካድሬዎች ተቃውሞ አጋጠመው። ይህንኑ ተከትሎ ከሳምንት በፊት በአንዳንድ የትምህርት ተቋማት ብልጭ ድርግም ሲል የነበረው ተቃውሞ እየጠነከረ መጣ። የክልሉ የጎልጉል ምንጭ “ተቃውሞው እንደሚጨምር፣ ካድሬውም የተቃውሞው ስውር አጋር እንደሆነ፣ በመረጃ ትንተና አስቀድሞ ይታወቅ ነበር። በዚሁ መሰረት አስቀድሞ አመጹን ማምከን ካልተቻለ የማያዳግም ርምጃ እንዲወሰድ ለፌዴራልና ለመከላከያ አባላት መመሪያ ተሰጥቷል”።
የሰላማዊ ሰልፍ በሚጀመርበት አካባቢ ሌላውን “ሊያስተምር” የሚችል ከበድ ያለ የሃይል ርምጃ እንዲወሰድ በተላለፈው መመሪያ መሰረት ተግባራዊ ቢደረግም ረብሻውና የተቃውሞ እንቅስቃሴው እየሰፋ መሄዱን የጎልጉል መረጃ አቀባይ ይናገራሉ። ከከተማ ወደ ከተማ እየሰፋ የሄደው ተቃውሞ፣ የተቃውሞው አካል በሚመስሉ የስለላ ሰራተኞች በሚያቀብሉት መረጃ መሰረት ለማስታገስ ቢሞከርም አለመቻሉ ኢህአዴግ ውስጥ ጭንቀት ፈጥሯል።
የኦህዴድ አባላት በከፍተኛ አመራር ላይ ያሉትን ጨምሮ ተመሳሳይ አቋም ያልያዙበት አዲሱ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይ በኦሮሚያ የተላዘበውን የፖለቲካ ችግር ሊያባብሰው ይችላል በሚል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኢህአዴግ የፖሊስ የመከላከያ ሃይላት ከልዩ መመሪያ ጋር በተጠንቀቅ እንደቆሙ ምንጩ አመልክተዋል። ይሁን እንጂ በኦህዴድ የታችኛው የቀበሌ መዋቅር ጭምር ተቃውሞው ስለሚደገፍ የአቋም መንሸራተት ሊፈጠር ይችላል የሚለው ስጋት ከፍተኛ መሆኑንንም አልሸሸጉም።
ከተለያዩ የማህበረሰብ አምዶች ሲደመጥ እንደሰነበተውና ሚያዚያ 22፤2006 (ኤፕሪል 30/2014) ቀን የአሜሪካ ሬዲዮ ከስፍራው ሰዎችን በማነጋገር እንደገለጸው ጅማ፣ አዳማ፣ ነቀምት፣ አምቦ፣ ሃሮማያ፣ ድሬዳዋ፣ በመሳሰሉት ከተሞችና የትምህርት ተቋማት ማህበረሰብ ላሰሙት የተቃውሞ ድምጽ የተሰጣቸው ምላሽ ዱላና እስር ነው። ከአምቦ በስልክ ስለሁኔታው የተናገሩ እንዳሉት አላፊ አግዳሚው ሳይቀር “ተጨፍጭፏል”።
በተጠቀሰው ቀን ረፋዱ ላይ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ ከሰዓት በኋላ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተቃውሞ ሲወጡ የመከላከያ አንጋቾችና የፌዴራል ፖሊስ አባላት በወሰዱት የሃይል ርምጃ በርካቶች መቁሰላቸውን፣ በነፍስ አውጪኝ አጥር ዘለው የሸሹትን በማሳደድ ጨፍጭፈዋቸዋል። እኚሁ ሰው በስልክ እንደተናገሩት “ሸሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው የመጡትን ተማሪዎች ለምን ቤትህ አስገባህ ተብዬ ተጨፈጨፍኩ፣ ነፍሴን ለማትረፍ መሬት እየተንከባለልኩ ጮህኩ። ሁለት ልጆቼን ወሰዱ” በማለት ሃዘናቸውን ገልጸዋል። የአምቦ ቤተመንግሥትም እስረኛ እንደሞላው አመልክተዋል።
ለማቅረብ ከያዟቸው ሶስት ጥያቄዎች መካከል አንዱ “ፊንፊኔ ያለው የአጼ ሚኒሊክ ሃውልት ይነሳ የሚል ነው” በማለት ፈርቶ እንደተሸሸገ የተናገረ ተማሪ ከአዳማ ለቪኦኤ ተናግሯል። የቪኦኤው ዘጋቢ ባለስልጣናትን ለማነጋገር ሞክሮ እንዳልተሳካለት፣ በመጨረሻም ከኦሮሚያ ምክር ቤት ያገናቸው ሰው መልስ ሳይመልሱ እንደመሳቅ እያሉ ስልኩን እንደዘጉት በግብር አሳይቷል።
ከምርጫ 97 በፊት አዳማን የኦሮሚያ ዋና ከተማ መደረጓን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ችግር ከምርጫ 97 በኋላ ቀውሱ እልባት እንደተበጀለት ይታወሳል። በወቅቱ በሜጫና ቱለማ ማህበር አስተባባሪነት አዲስ አበባ ላይ የተካረረ ሁኔታ ተፈጥሮ እንደነበርም አይዘነጋም። በዚያን ወቅትም የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ድሪቢን ጨምሮ በርካቶች ታስረው ነበር። ኢህአዴግ አቋሙን ለምርጫ ቀውስ ማርገቢያ በሚል ሲቀይር፣ ድርጊቱን አስቀድመው በመቃወማቸው የተገረፉ፣ የታሰሩና ከስራ እንዲሰናበቱ የተደረጉ ካሳ ሊሰጣቸው እንደሚገባ በወቅቱ ተገልጾ ነበር።
አገሪቱ ላይ ከተንሰራፋው የተለያየ ችግር ጋር ተዳምሮ በኦሮሚያ የተጀመረው ተቃውሞ እንዳይካረር ስጋት የገባቸው ክፍሎች “ኢህአዴግ ጉልበት እየተጠቀመ የሚዘራውን ቂምና ቁርሾ ካላቆመ፣ ጠብመንጃ እጄ ላይ ነው በማለት የሚፈጽመውን ግፍ በማቆም ለእርቅ ካልሰራ አሁን ባለው ሁኔታ ነገሮች ከቁጥጥር ሊወጡ” እንደሚችሉ ማስጠንቀቂያ ይሰጣሉ፤ ጂኒው አንዴ ከሳጥኑ ከወጣ በኋላ ልዩነት ሳያደርግ የሚያመጣው መዘዝ ለህወሃት/ኢህአዴግና በቅድሚያ ከዚያም ለሥርዓቱ ባለሟሎች በተዋረድ የሚባላ እሣት እንደሚሆን ታስቦ ካሁኑ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል ይላሉ።

Wednesday, April 30, 2014


ሰበር ዜና!!!

በሕገ ወጡ መጅሊስ ውስጥ መፈንቅለ ስልጣን መደረጉ

 ተነገረ!

ፕሬዚዳንቱ በሌሉበት ሥልጣናቸውን ተነጥቀዋል!


ድምፃችን ይሰማ



ረቡእ ሚያዝያ 22/2006

በዶ/ር ሽፈራው እና በደህንነት መስሪያ ቤቱ አማካኝነት የሚመሩት የአዲስ አበባ እና የአማራ መጅሊስ አመራሮች መፈንቅለ ሥልጣን ዛሬ መፈጸማቸውን የቅርብ ምንጮች ገለጹ! ይኸው መፈንቅለ ስልጣን የፌዴራል መጅሊስና የአዲስ አበባ መጅሊስን ያመሰ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በዛሬው መፈንቅለ ስልጣን የፌዴራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸኽ ኪያር ሸኽ መሀመድ አማን፣ የፌዴራል መጅሊስ ዋና ጸሀፊ አቶ ሙሀመድ አሊ፣ ከአዲስ አበባ መጅሊስ ደግሞ ኢንጂነር ተማምና ሌላ አንድ ሀላፊ መነሳታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ከስልጣናቸው ተነሱ የተባሉት ፕሬዝደንቱ ሸኽ ኪያር በአሁኑ ሰአት ከአገር ውጪ በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በዛሬው መፈንቅለ ሥልጣን በሸኽ ኪያር ቦታ የኦሮሚያ ክልል ተወካዩ መተካታቸው ሲገለጽ፣ የአማራው ክልል ተወካይም የኡለማ ም/ቤቱን መረከባቸው ተሰምቷል፡፡

በዚህ ዛሬ ተጠናቀቀ በተባለው መፈንቅለ ስልጣን ታጋይ የነበሩት የትግራይ ተወካይና ም/ፕሬዝደንት ሸኽ ከድር፣ የአዲስ አበባው መጅሊስ ፕሬዝደንት ዶ/ር አህመድ እና የአማራ መጅሊስ ተወካይ አይነተኛ ሚና እንደነበራቸው የታወቀ ሲሆን ከኋላቸውም ዶ/ር ሽፈራውና የደህንነት ሀላፊዎች ሲመሩት ቆይቷል፡፡ የስልጣን ሽኩቻው ረዘም ላለ ጊዜ የቆየ ሲሆን በድሬዳዋ ከተማ በተካሄደው ጉባኤ ላይም ፈንድቶ እስከመውጣት ደርሶ ነበር፡፡ የሽኩቻው ዋነኛ ምክንያትም ከመንግስት በኩል በግዳጅ ህዝበ ሙስሊሙ ላይ ለመጫን ሲሞከር የነበረው የአህባሽ አስተሳሰብ ዳግም በህዝበ ሙስሊሙ ላይ መጫኑ እንዲቀጥል በሚፈልጉት ወገኖች እና ‹‹ህዝበ ሙስሊሙ ሲቃወመው የነበረው የግዳጅ ጠመቃ ቆሞ መጅሊሱ ሁሉንም ሙስሊም በአንድነት ሰብስቦ እና አቻችሎ መቀጠል አለበት›› በሚሉት ዛሬ ከስልጣን በተወገዱት ሀላፊዎች መካከል ያለው የአቋም ልዩነት መሆኑ ታውቋል፡፡

እስካሁን በነበረው ሂደት የመጅሊሱ ፕሬዝደንት ‹‹መጅሊሱ ህዝበ ሙስሊሙን የሚጠቅም እና በሰላም እንዲኖር የሚያደርግ እንጂ ችግር ውስጥ የሚያስገባ አካል መሆን የለበትም›› የሚል ፅኑ አቋም ይዘው የነበረ ሲሆን በሸኽ ከድር በሚመራው ቡድን እየተደረገ ያለውን ህዝበ ሙስሊሙን ዳግም ወደ ተቃውሞ ሊያስገባ የሚችል ትንኮሳ በመቃወምም ለተለያዩ የመንግስት አካላት ደብዳቤ መፃፋቸው ታውቋል፡፡

በሕገ ወጡ መጅሊስ ውስጥ ከላይ እስከታች የሚታየው የስልጣን ሽኩቻ የተቋሙን አመራር ሕገ ወጥነት አመላካች ከመሆኑም በላይ በመንግስት የተሰጠውን የቤት ስራ ለመፈጸም የተሰባሰበ ቡድን መሆኑንም ክስተቱ እማኝነት ሰጥቷል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎችና ማብራሪያዎች በነገው እለት ይኖሩናል - ኢንሻአላህ!

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!


በዋልድባ ገዳም እየተካሄደ ያለው እምነትን የማፍረስ ዘመቻ ዛሬም እንደቀጠለ በቦታው የሚገኙ መነኮሳት በምሬት ገለፁ፡፡


ድምጻችን ይሰማ ዘኦርቶዶክስ


ቀደም ሲል ወደ 20 የሚጠጉ ገዳማትን ለማፍረስ ተንቀሳቅሶ የነበረው የኢህአዴግ አፍራሽ ሀይል በመነኮሳት ፣ በባህታውያን፣… ፀሎትና በአካባቢው በሚገኙ ተቆርቋሪዎች ሲከሽፍበት የዘጉ ባህታውያንና ጨምሮ በርካቶችን በማሰር፣ በመደብደብ፣በማፈናቀልና በማንገላታት ጉዳት ማድረሱ ይታወቃል፡፡ በዚህም ያተረፈው 2ቱን ‹መሪዎችን› መለስ ዜናዊና ገ/ መድህን/ጳውሎስ ፣ በቦታው የሄዱ መሀንዲስና ሰራተኞችን፣ ጠበንጃ አንጋቾችን ጨምሮ በርካቶችን በሞት ሲነጠቅ በራሱ ላይ ከፍተኛ ችግር አድርሷል፡፡ ቃሌማ የተባለ የገዳሙ ዙሪያ በርካት ገበሬዎችን አፈናቅሎ ‹የስኳር› ተክል መዝራቱ ይታወቃል፡፡
ይሆንና በየጊዜው ኪሳራን እየተከናነበ በሀገርና በሕዝብ ላይ በደል የሚያደርሰው ኢህአዴግ በ16/ 08/ 2006 ዓ. ም በዕለተ ሀሙስ ማይ ለበጣ በተባለ ቦታ የገዳማትን ሰዎች ሰብስቦ፡-
1ኛ፡- ድልስ ቆቃ አቡነ- አረጋዊ ገዳም፣
2ኛ፡- መሀር ገፅ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም፣
3ኛ፡- እጣኖ ማርያም ገዳም ፣….‹ለስኳር ልማት› እንዲፈርሱ በቀጣይ ደግሞ ማይጋባ ቅ/ ጊዮርጊስ ‹ ይነሳሉ› የሚል ሀሳብ ሲያቀርብ በርካታ ተቃውሞ ቀርቦ ከፍተኛ ውዝግብ ፈጥሯል፡፡
በመህል የሰገሰጋቸው አሰሮች የድጋፍ ድምፅ ሲያሰሙ መነኮሳትና መናንያን ተቃውሞሙን በማጠናከራቸው ለግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ. ም ተቀጥሯል፡፡ በዚህም የዋልድባ ገዳም ተቆርቋሪ የሆናችሁ ሁሉ ድምፃችሁን አሰሙልን ሲሉ ተማፅነዋል፡፡


ለወይዘሮሪት ኢህአዴግዬ ሰው ማሰር ሻሽ ሸብ ከማድረግ እኩል ቀላል አይደለምን?! – አቤ ቶክቻዉ

ወዳጄ….
በሩቁ የምታውቀው ወዳጅህ ሲታሰር፤ አሳሪዎቹ የሚደረድሩልህ ምክንያት ትንሽ እውነት ሊኖረው ይችላል ብለህ ልታስብ ተችላለህ ከዛ አሳሪዎች መቼም ማሰር አይታክታቸውም አይደል፤ ቀረብ የሚልህ ወዳጅህን ደግሞ ያስራሉ፤ ማሰር ብቻም አይደል ያለ የሌላቸውን ምክንያቶች በቴሌቪዥን በራዲዮ አከታትለው ይነግሩሃል ይሄኔ ግራ ትጋባለህ …መንግስትን ያህል ነገር እንዲህ አይን አውጥቶ ሊዋሽ ይችላል….. ወይስ ወዳጄን በቀጡ አላውቀውም ነበር ብለህ ይምታታብሃል…
የኔ ጌታ አሳሪ ጠዋት ቀበቶውን ካሰረ ሰዓት አንስቶ ሙሉውን ቀን፤ “ደግሞ ማንን ልሰር….” ሲል ነው የሚወለው። እና እያለ፣ እያለ ከራስህ በላይ አውቀዋለው የምትለውን ወዳጅህን ወይም እራስህን ጥርቅም አድርጎ ያስራል። ይሄኔ የፈለግ ምክንያት ቢደረደርልህ አሳሪውን ልታምን እንደማትችል የታወቀ ነው ሀቁ ያለው ራስህ ጋ ነዋ!
እናም ወዳጄ…
በተለይ እንደ ኢህአዴግ ያለ የማሰር ሱስ ያለበት አሳሪ በሩቁ የምታውቃቸውንም በቅርብ የምታውቃቸውንም አስሮ ምክንያት ሲደረድር ወዳጆችህን አተጠራጠር እውነቴን ነው የምልህ መንግስታችን ሰዎችን ሲያስር ጥጃ የማሰር ያክል አይጨንቀውም። ለዚህ ደግሞ አጥጋቢ ምክንያት ሲፈልግ አየገኝም፤ በቃ የአይንህ ቀለም ካላማረው ያስርሃል።
የ ዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን የማውቃቸው ማንም ሰው የታሰረ እነደሆነ መዝገብ አገላብጠው መታሰሩ ከህግ አንጻር፣ ከህገ መንግስት አንጻር፣ ከሞራል አንጻር፤ እያሉ የህሊና ፍርድ ሲሰጡ ነው። ሙስሊም ሳይሉ ክርስቲያን ሳይሉ ኦሮሞ ሳይሉ ጋምቤላ ሳይሉ ያለ ለዩነት ጆሯቸው የደረስ አይናቸው ያየውን ኢፍትሃዊነት ሲያወግዙ ነው። ደግሞ ሲያውግዙ ብቻ አይምሰልህ መንግስት የሚሰራቸው መልካም ነገሮችም እውቅና ሊሰጠው ይገባል፤ ጽንፈኛ መሆን ተገቢ አይደልም ሲሉም ይውቅሱሃል።
ዛሬ መንግስት እነዚህን ወጣቶችን ሰባስቦ አስሯቸዋል። (ለወይዘሮሪት ኢህአዴግዬ ሰው ማሰር ሻሽ ሸብ ከማድረግ እኩል ቀላል ነው (በሌላ ቅንፍ ኢህአዴግዬን ወይዘሮሪት ያልኩታ ታግባ አታግባ በቀጡ ሰላላወቅሁ ነው፤ ግራ ስታገባን ግን በድንብ አውቃታለሁ… ሃሃ))
እኔ በአስሩም ጣቴ እፈርማለሁ፤ ዘጠኙም ጋዜጠኞች እና አስተያየት ሰጪዎች የታሰሩት እንደ ሰው በማሰባቸው እና በሀገራችን ጉዳይ ያገባናል በማለታቸው ብቻ ነው!
እንደዚህ የምልህ መንግስቴ ከሀገሬ አሯሩጦ ስላስወጣኝ ቂም ይዤ አለመሆኑን ድንጋይ ነክሼ እምልልሃለሁ!


የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ህግን ለማስከበር በመጣራቸው

 ተጨማሪ ቅጣት ተጣለባቸው!!



ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በቅስቀሳ ላይ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በ1000 (አንድ ሺህ ብር) ዋስ እንዲወጡ መወሰኑን ተከትሎ ‹‹እኛ ነጻ ነን፡፡ ገንዘብ አስይዘን እንወጣም፡፡ ስራችን ህግ ማስከበር እስከሆነ ድረስ እየታሰርንም ቢሆን ህግ እናስከብራለን፡፡ በመሆኑም ነጻ እስካልተለቀቅን ድረስ እሰሩን፡፡›› በማለታቸው ተጨማሪ ክሶችና ቅጣቶች እየተጣለባቸው ነው፡፡ 
በትናትናው ዕለት ሜሮን አለማየሁና ትግስት ወንዲፍራው ‹‹ግቢ በመረበሸ›› ተጨማሪ ክስ መከሰሳቸው ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ወቅት በቤላ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙ 14 ያህል የሰማያዊ ፓር አመራሮችና አባላትም ተመሳሳይ ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን ባለፈው ከፍላችሁ ውጡ ከተባሉት 1000 (አንድ ሺህ ብር) በተጨማ 600 (ስድስት መቶ ብር) ጨምረው ከፍለው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡
እነዚህ አመራሮችና አባላት መጀመሪያ የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የነበሩ ቢሆንም እስረኛውን በማሳመጽና በመረበሽ ከመከሰሳቸውም በተጨማሪ ወደ ቤላ ፖሊስ ጣቢያ ተዛውረዋል፡፡ በወቅቱ ድብደባና ማዋከብ እንደደረሰባቸው የሚናገሩት ታሳሪዎቹ ‹‹ህግን ለማስከበር የምናደርገውን ጥረት እንደ ህገ ወጥነት ተቆጥሮ ተጨማሪ ክስና በደል ቢፈጸምብንም እኛ ህግ ማስከበራችንን እንቅጥላለን›› ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ በጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙትና ዛሬ ስምንት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እያንዳንዳቸው 5500 ብር አስይዘው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ታሳሪዎቹ ይህንን ውሳኔ በመቃወም ‹‹ነጻ ካልተለቀቅን አንወጣም!›› ያሉ ሲሆን ከዳኛው የተሰጣቸው መልስ እንዳሳዘናቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ዳኛውና አቃቤ ህጉ ተመካክለው ነው የገቡት፡፡ በእያንዳንዳችን 5500 ብር እንድንከፍል ሲፈርዱ፤ ‹እኛ ተማሪዎችና የመንግስት ሰራተኞች ነን ከየትም አምጥተን መክፈል አንችልም!› አልናቸው፡፡ እነሱ ልክ አንድ ሰው እቃ ሲገዛ እንደሚከራከረው ‹በቃ! 2000 ብር ይሁንላችሁ› አሉን፡፡›› ያሉት ታሳሪዎቹ በህግ ሳይሆን በዘፈቀደ እየተሰራ መሆኑ አሳዝኗቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ‹‹ህገ ወጥ ቢሆንም በሌላ አካባቢ የታሰሩት የእኛ ጓደኞች 1000 ብር ነው እንዲከፍሉ የተወሰነባቸው፡፡ የእኛውን ለምንድን ነው 5500 ያደረጋችሁት?›› ብለው ሲጠይቁ ዳኛው ‹‹ቅጣቱ ከጣቢያ ጣቢያ ይለያያል፡፡›› የሚል አስገራሚ መልስ እንደሰጧቸው ገልፀዋል፡፡

Tuesday, April 29, 2014

''ድምፃችን ይሰማ'' አዲሱን የትግል ምዕራፍ አስመልክቶ ህዝበ ሙስሊሙ  የጋራ


 ግንዛቤ ይኖረው ዘንድ የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል::


ኢንተርኔት ተጠቃሚ ላልሆነው አብዛኛው የህብረተሰባችን ክፍል በወረቀት 

አባቶ በመስጠትና የድምፅ መልዕክቱን በማስደመጥ ኃላፊነታችንን እንወጣ!!!


ሙሉ  ፅሁፉን  ከዚህ  በፊት  ፖስት  ከተደረገው  ላይ ማግኘት  ይችላሉ  . . . . 

''ምድር ህላዌዋ ከተቦካበት ቅፅበት አንስቶ በለውጥ ምህዋር ላይ እየተሸከረከረች ትገኛለች፡፡ ቀኑ ሰዐቱን ጠብቆ ሲመሽ ብርሀን በጨለማ ይለዋጣል፡፡ ምሽቱ ተራውን ለቀን ሲያስረክብ ደግሞ ጨለማው በብርሃን ይለወጣል፡፡ ምድር ሁሌም በለውጥ ሀዲድ ላይ ትከንፋለች፡፡ ዛሬ ከትላንት፣ ነገም ከዛሬ ለውጥን ይቀባበላሉ፡፡ የሰው ልጅ የህይወት ዑደት ስለ ለውጥ ተፈጥሮዊነት አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡ ከአንቀልባ እስከ ከፈን በሚዘረጋው የህይወት ጅረት የሰው ልጅ ሲፈስ በበርካታ የለውጥ ድልድዮች ስር ያልፋል፡፡ . . . ''

መልእክት - ቁጥር  http://goo.gl/PtMfJt 


''ላለፉት ሁለት አመታት አንግበን የተነሳናቸው ሶስቱ የመብት ጥያቄዎች ምላሽ ያገኙ ዘንድ ደከመን ሰለቸን ሳንል በትዕግስት እየታገልን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ እነዚሁ ያሳለፍናቸው የትግል አመታት ሂደታቸው ፍፁም ያማረ ቢሆንም ሶስቱን ጥያቄዎች ማስመለስን ገደብ አድርገን የተጓዝናቸው የትግል ጎዳናዎች ግን የምንፈልገው ቦታ ሊያደርሱን አልቻሉም፡፡ መንግስትም ጉዳዩን አጢኖ እልባት እንዲያገኝ ከመትጋት ይልቅ በአጉል ስም ማጥፋት ተጠምዶ ትግሉን በሀይል ለማስቆም እየባተለ ይገኛል፡፡ሙስሊሙ ህብረተሰብ የሀይል እርምጃው ሳይገታው ‹‹ጥያቄዎቹ አለተመለሱም›› ሲል ትግሉን ቢቀጥልም የመንግስት አፀፋ ግን ለሞት እና ለጅምላ እስር ዳርጎታል፡፡ ቀን በቀን በተተካ ቁጥር የመንግስት እምቢተኝነትና የሚወሰደው እርምጃ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አልታየም፡፡ ይህም ሆኖ ግን ትግሉ ከተጀመረበት ቅፅበት አንስቶ ባሳለፋቸው ሂደቶች የተከፈሉት ከፍተኛ መስዕዋትነቶች በርካታ የድል ፍሬዎችንም አስገኝተዋል፡፡ . . . ''

መልእክት - ቁጥር 2  http://goo.gl/VZLYjv 

''የኢትዮጲያ ሙስሊም በእምነቱ ላይ የተቃጣውን የአስተሳሰብና የመብት ጥሰት ዘመቻ ለመመከት፣ አስተሳሰቡን በኢስላማዊ አስተሳሰብ ለማረቅ፣ የሕግ ጥሰቱ በህግ ማእቀፍ ዕልባት ያገኝ ዘንድ ስላማዊ ትግል ሲጀምር መሪዎችን ከመፍጠሩም በላይ የተመሪነትን ስርዓት ለሀገራችን ታሪክ አዲስ በሆነ መልኩ ማሳየትና ማስተዋወቅ ችሏል፡፡ ሕዝቡ የፈጠራቸውን መሪዎች ያለጥርጥር ተከትሏል፡፡ ትዕዛዛቸውን ያለ ፍርሀት ተግብሯል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ በባለቤትነት በሚመራው በዚሁ የመብት ማስከበር ስላማዊ ትግል ሂደት ውስጥ ልክ እንደማንኛውም ትግል ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፏል፡፡ በርካታ መስዕዋትነት ከፍሏል፤ እየከፈለም ይገኛል፡፡ እስከ ድል ጫፍ በተዘረጋው የትግል ድልድይ ሲያልፍ እስራት፣ ድበደባ፣ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ፣ ስም ማጥፋትና መገለል ደርሶበታል፡፡ እነዚህ የትግል ገፅታዎች ህዝበ ሙስሊሙ በትግሉ መባቻ ላይ ከነበረው ቁመና ከፍ ያለ ተነሳሽነትና ፅናት ላይ እንዲገኝ አስችለውታል፡፡ በዚህም የአስተሳሰብ እመርታና የባህሪ ለውጥ ከማምጣቱም ባሻገር በትግሉ ሂደትም ላይ ተገቢ የሆነ የለውጥ ፍላጎት አሳድሮበታል፡፡. . .''

መልእክት - ቁጥር 3  http://goo.gl/zqdaiz 

''በሃምሌ 2003 የአህባሽ ጠመቃ ዋነኛ መንስኤነት የተጀመረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የመብት ማስከበር ትግል ትላልቅ እርከኖችን አልፎ መጥቷል፡፡ አሁን ወደ ቀጣዩ እርከን የሚሸጋገርበት ወሳኝ ወቅት ላይ ይገኛል፡፡ እስካሁን በነበረው ሂደት ትግሉ ይዞት ከተነሳቸው ሶስት ጥያቄዎች አለመመለስ ውጭ እጅግ ውጤታማ ሂደት ነበር፡፡ ምናልባት ጥያቄዎቹ ቢመለሱ ሊሰጡት ከሚችሉት ጥቅም በላይ ሌሎች ትልልቅ ፋይዳዎችን ለኡማው አበርክቷል፡፡ ከውጤቶቹ አንዱ ደግሞ ህዝባችን መብታችንን ማስከበር እና ከውስጥ ጉዳያችን የመንግስትን ጣልቃ-ገብ እጆች ማስወጣት ጊዜ ሊሰጠው እንደማይገባ በይፋ መናገር የሚችልበት ደረጃ ላይ መድረሱ ነው፡፡. . . ''

መልእክት - ቁጥር 4  http://goo.gl/H2JjNn

TPLF/EPRDF charges nine bloggers and journalists with inciting violence!!




(Reuters) – Ethiopia has charged six bloggers and three journalists with attempting to incite violence, their supporters said on Monday, prompting accusations from rights groups that the government is cracking down on its critics.
All nine defendants, including freelance journalists Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, appeared in court on Sunday after they were rounded up by police on April 25 and April 26, their colleagues told Reuters.
On Monday, Human Rights Watch (HRW) called on U.S. Secretary of State John Kerry, who visits Ethiopia on Tuesday, to press the government to “unconditionally release” all the defendants, but Addis Ababa dismissed the criticism of the case.
“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, HRW’s deputy Africa director.
“The timing of the arrests – just days before the U.S. secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech,” she said in a statement.
In 2012, Addis Ababa sentenced a prominent blogger and five other exiled journalists to between eight years to life on charges of conspiring with rebels to topple the government.
In the new case, a colleague of Tesfalem said security officials in plain clothes searched his house and confiscated several materials before taking him to a detention center.
An Ethiopian government official defended the case against the nine, saying it had nothing to do with muzzling the media.
“CRIMINAL ACTIVITIES”
“These are not journalists. Their arrest has nothing to do with journalism but with serious criminal activities,” Getachew Reda, an adviser to Prime Minister Hailemariam Desalegn, said.
“We don’t crack down on journalism or freedom of speech. But if someone tries to use his or her profession to engage in criminal activities, then there is a distinction there,” Getachew told Reuters.
Critics say Ethiopia – sandwiched between volatile Somalia and Sudan – regularly uses security concerns as an excuse to stifle dissent and clamp down on media freedoms.
They also point to an anti-terrorism law, passed in 2009, which stipulates that anyone caught publishing information that could incite readers to commit acts of terrorism can be jailed for between 10 and 20 years.
Addis Ababa says the law aims to prevent “terrorist attacks” as it is fighting separatist rebel movements and armed groups.
A court in Addis Ababa adjourned the hearing for the group of bloggers and journalists until May 7 and 8.
Kerry will meet Prime Minister Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom in Addis Ababa to discuss peace efforts in the region and to strengthen ties with Ethiopia, State Department spokeswoman Jen Psaki said in a statement.
The State Department says the aim of Kerry’s African tour – which will also take in Democratic Republic of Congo and Angola – is to promote democracy and human rights.
(Editing by James Macharia and Gareth Jones)
April 29, 2014

Ethiopian Authorities lie about crackdown against Free Speech!!


AFP – Ethiopia said Tuesday several people had been arrested on charges of “serious criminal activities”, but rights groups identified those detained as journalists and bloggers targeted in a sweeping crackdown against free speech.
“They are suspected of some serious crimes, and the police are investigating,” government spokesman Getachew Reda told AFP, without providing details of the alleged crimes.
The journalists and a group of bloggers known as “Zone 9″ were arrested last week, prompting an outcry from rights groups.
The Committee to Protect Journalists (CPJ) called the arrests “one of the worst crackdowns against free expression” in the country, while Amnesty International said it was part of a “long trend of arrests and harassment of human rights defenders, activists, journalists and political opponents.”
Leslie Lefkow of Human Rights Watch said the “arrests signal, once again, that anyone who criticizes  the Ethiopian government will be silenced”, and called for their immediate release.
The arrests come ahead of a visit this week by US Secretary of State John Kerry.
“The timing of the arrests — just days before the US Secretary of State’s visit — speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech,” Lefkow added.
The bloggers Zone 9 website, reportedly named after the prison where political detainees are held, listed the names of nine people arrested, saying they were charged with having worked with foreign human rights activists to foment violence or instability.
But the government dismissed the rights groups, and said those arrested were not detained for their work as journalists.
“We don’t take orders from Human Rights Watch,” Getachew said. - Free speech ‘a crime’ -
An opposition group staged a protest on Sunday following the arrests, calling for “greater liberties and a true democracy” in Ethiopia, but police shut the 200-person demonstration down soon after it started.
HRW said 20 members of the political opposition Semayawi or “Blue” party have also been arrested since Friday, although there has been no official confirmation of exact numbers.
“With the latest arrests, Ethiopian authorities are turning the peaceful exercise of free expression into a crime,” the CPJ’s Tom Rhodes said in a statement.
Amnesty said the group had only restarted blogging last week after suspending their work for the past six months, accusing the government of harassment.
Ethiopia has been accused of cracking down on independent media and has doled out several heavy sentences for journalists charged under the controversial anti-terror legislation, which rights groups have called vague and far-reaching.
“With still a year to go before the general elections, the Ethiopian government is closing any remaining holes in its iron grip on freedom of speech, opinion and thought in the country,” said Amnesty’s Claire Beston.
In 2011, two Swedish journalists were sentenced to 11 years in jail under the law, but were later pardoned after serving 15 months.
Ethiopia has one of the most closed press environments in the world, the CPJ says. It calculates that at least 49 journalists have been forced into exile, the third worst after Somalia and Iran.
@Alula Zewge

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትግል መሪ የሆነው ''ድምፃችን ይሰማ'' የፌስቡክ ፔጅ

 ለአዲሱ የትግል ምዕራፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንቅስቃሴ ጀመረ!!!

''ድምፃችን ይሰማ'' አዲሱን የትግል ምዕራፍ አስመልክቶ ህዝበ ሙስሊሙ  የጋራ

 ግንዛቤ ይኖረው ዘንድ የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል::

መልዕክት ቁጥር 4 እነሆ! 

#EthioMuslimStruggle 
አዲሱን የትግል ምእራፍ አስመልክቶ የጋራ ግንዛቤ እንዲኖረን የተላለፈ መልእክት - ቁጥር 4

የቀጣዩ የትግል እርከን መነሾዎች!
ማክሰኞ ሚያዝያ 21/2006

በሃምሌ 2003 የአህባሽ ጠመቃ ዋነኛ መንስኤነት የተጀመረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የመብት ማስከበር ትግል ትላልቅ እርከኖችን አልፎ መጥቷል፡፡ አሁን ወደ ቀጣዩ እርከን የሚሸጋገርበት ወሳኝ ወቅት ላይ ይገኛል፡፡ እስካሁን በነበረው ሂደት ትግሉ ይዞት ከተነሳቸው ሶስት ጥያቄዎች አለመመለስ ውጭ እጅግ ውጤታማ ሂደት ነበር፡፡ ምናልባት ጥያቄዎቹ ቢመለሱ ሊሰጡት ከሚችሉት ጥቅም በላይ ሌሎች ትልልቅ ፋይዳዎችን ለኡማው አበርክቷል፡፡ ከውጤቶቹ አንዱ ደግሞ ህዝባችን መብታችንን ማስከበር እና ከውስጥ ጉዳያችን የመንግስትን ጣልቃ-ገብ እጆች ማስወጣት ጊዜ ሊሰጠው እንደማይገባ በይፋ መናገር የሚችልበት ደረጃ ላይ መድረሱ ነው፡፡

መንግስት ጥያቄዎቹን ላለመመለስ እየተከተለው ያለው አካሄድ ሙስሊሙ እንደዜጋ ከሚጋፈጣቸው ዘርፈ ብዙ ችግሮች በተጨማሪ እምነቱን ብቻ መሰረት ያደረገ ነጥሎ የማጥቃት ዘመቻውን በዕቅድ ይዞ እንደሚሰራው መላው ህዝብ በማያሻማ ሁኔታ መረዳቱ ለዚህ ደረጃ መደረስ ዋና ምክንያት ነው፡፡ የጥያቄዎቻችን ቀላል ይዘት፣ ያቀረባቸው መላው ሙስሊም ከመሆኑ እና ከሁለት አመታት በላይ በፅናት ከመዝለቁ ጋር ተዳምሮ መልስ ሊነፈግ የቻለው በአንድ እና አንድ ምክንያት ነው፡- ይኸውም ሃምሌ 2003 ይፋ የሆነው የመንግስት ዕቅድ የአጠቃላይ ዘመቻው አንዲት ማሳያ ብቻ በመሆኑ! ይህ ማሳያ ፊት ለፊት የሚታገል ህዝብ ባያጋጥመው የት ድረስ እንደሚጓዝ መገመት አይከብድም፡፡ በትግል ውስጥ ላለ አንድ ማህበረሰብ ደግሞ ይህንን መረዳት ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡

ሰላማዊ የመብት ትግላችን ሶስት ውስን ጥያቄዎችን አስቀድሞ ሲመርጥ ጥያቄዎቹ የሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ብቸኛ ሃገራዊ አጀንዳዎች ስለሆኑ አልነበረም፡፡ የህዝበ ሙስሊሙ የመታገል አቅም እና አካሄድ ‹‹አምባገነኖችን ተክቼ ፍትህን በየደረጃው ለማስፈን ቆሜያለሁ›› የሚልን መንግስት ሶስት ጥያቄዎችን እንዲመልስ ለማድረግ እንደማያንስ አስቀድሞም ይታወቅ ነበር፡፡ ጥያቄዎቹን ውስን ማድረግ ግድ የሆነው መንግስት ሃገር ለማስተዳደር፣ ህዝብ ደግሞ ሙሉ ዜግነት እንዲሰማው መሟላት ያለባቸው መሰረታዊ መብቶች ከአጠቃላይ የሃገሪቱ ማህበረ-ፖለቲካ ጉዞ ጋር እንደሚፈቱ በማመን ነበር፡፡ እነዚህ መሰረታዊ መብቶች አሁንም ከአጠቃላይ የሃገሪቱ ሂደት ጋር ተዳምረው የሚታዩ ቢሆንም ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ መብቶቹን ከሌላ አካል እንደሚበረከቱለት ገፀ በረከቶች አድርጎ የሚጠብቅበት እድልም ተስፋም አግባብም እንደሌለ የሁለት አመት ሰላማዊ ትግላችን ጥርት ባለ መልኩ አሳይቶናል፡፡

ዛሬ ላይ ባነሳቸው ውስን ጥያቄዎች ሽፋን እየተገፈፉ የመጡት ሌሎች መሰረታዊ መብቶች አካሄዳቸውን ለመቀልበስ የማይቻልበት ደረጃ ከመድረሱ በፊት ህዝበ ሙስሊሙ እውነታውን ሊረዳ፣ ተረድቶም ተግባራዊ እርምጃ ሊወስድ ግድ ይለዋል፡፡ የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄም ነው፡፡ ከሁለት አመታት በፊት ከህዝብ ከተሰበሰቡት በርካታ ጥያቄዎች ሶስት ሲመረጡ በወቅታዊነታቸው፣ በአንገብጋቢነታቸው መሆን ያለባቸው እና መሆን የሚችሉ እንደሆኑ በመታመኑ ነው፡፡ እነዚያ ጥያቄዎቻችን ዛሬም አንገብጋቢ እና መሆን ያለባቸው ናቸው፡፡ ነገር ግን እነሱ እውን እንዲሆኑ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ ማድረግ የወቅታችን ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ግድ ነው፡፡

ህዝብ ባስቀመጠው ሰፊ የእፎይታ ጊዜ ውስጥ ሰላማዊ ትግላችንን አስመልክቶ ጥልቅ ፍተሻ እና ቀጣይ ጉዞን በሚመለከት ህዝብ አሳታፊ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ የፍተሻው አበይት ውጤት የሚጠቁመው ያነሳናቸውን ሶስት ጥያቄዎች ለማስመለስ የአቅምም ሆነ የአካሄድ ጉድለት አለመኖሩን ነው፡፡ በተቃራኒው ያለማቋረጥ እየደረሱ ያሉት የመብት ጥሰቶች አንድ ህዝብ ሊያነሳቸው ከሚችላቸው የሰላማዊ ትግል አጀንዳዎች ትልቁን ለማንሳት የሚያስገድዱ ነበሩ፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ግን ዛሬም እንደከዚህ ቀደሙ ብሶት መርሁን እንዳይስት አላደረገውምና ለጥያቄዎቹ አለመመለስ ጥያቄዎቹ የቀረቡበትን አግባብ እና የቀረቡለትን አካል መፈተሽ እንደሚያስፈልግ የጋራ ስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ በነዚህ ህዝብ አሳታፊ ፍተሻዎች እና የቀጣይ ጉዞ የማስቀመጥ ስራ የትግል ጥያቄዎቻችን አንድ... ሁለት... ሶስት... እየተባሉ ተነቅሰው የሚወጡ፣ በጊዜ እና በቦታ የተገደቡ ውስን ነጥቦች አይደሉም፡፡ ይልቁንም አስፈላጊው ነገር የችግሮቻችንን ምንጭ ታሳቢ ያደረገና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የሚካሄድ ሁሉን አቀፍ ጉዞ መሆኑ ግልጽ ሆኗል፡፡

የሰላማዊ ትግላችንን ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ መነሻ የሆነው እውነታ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ባለፉት ሁለት አመታት የከፈለው መስዋእትነትና ያዳበረውን አንድነት፣ ጥንካሬ፣ ትእግስትና ታዛዥነት በመጠቀም የበለጠ ተጠቃሚና ዘላቂ ወደ ሆነ ትግል ማሸጋገር መቻሉ ሲሆን በዝርዝር ድግሞ እንደሚከተለው ሊቀመጥ ይችላል፡-

•ሙስሊሙ ማህበረሰብ እየከፈለው ያለውን መስዋእትነት የበለጠ ውጤት-ተኮር ለማድረግ የሚያስችሉ ዘርፈ-ብዙ ስልቶችን በመንደፍ ሃይማኖታዊ መብታችንን ለማስከበር፣

•ህብረተሰቡ የታገለለት ዓላማ አካሄድ ሰላማዊ፣ ነገር ግን የተሟላ እንዲሆን ለማድረግ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት፣

•እየተከፈለ ያለው መስዋዕትነት ሰፊና ዘርፈ-ብዙ ፍላጎቶችን ሊሸፍን በሚችል መልኩ እንዲሆን ለማመቻቸት፣

•ሁሉም የህብረተስብ ክፍል ትዕግስትና ጥንካሬ ተላብሶ እንደየዘርፉ የሚቻለውን እንዲያበረክት በር ለመክፈት፣

በእነዚህ መነሻዎች የሚቃኘውን የህዝበ ሙስሊሙን ቀጣይ ሰላማዊ ትግል አስመልክቶ ከፊታችን ባሉት ተከታታይ ሳምንታት ሰፊ ግንዛቤ የማስጨበጥ እና የህዝብን አመለካከት መልሶ ለህዝብ የማንፀባረቅ ሰፊ ስራ ይኖራል፡፡ በዚህ ስራ ላይ መረጃዎችን በማሰራጨት፣ ትንተናዎችን በመስራት፣ ብዥታዎችን በማጥራት እና ለተግባራዊነታቸው በሙሉ አቅም በመስራት ረገድ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርግ እና የጀመርነውን ሰላማዊ ትግል ከጫፍ ለማድረስ የማይተካ ሚናውን እንደሚወጣ ይጠበቃል!

የትግል አቅጣጫ ማስገንዘቢያ መልእክቱን የድምጽ ትረካ ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ፡-
http://goo.gl/H2JjNn

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!