Wednesday, April 30, 2014


ሰበር ዜና!!!

በሕገ ወጡ መጅሊስ ውስጥ መፈንቅለ ስልጣን መደረጉ

 ተነገረ!

ፕሬዚዳንቱ በሌሉበት ሥልጣናቸውን ተነጥቀዋል!


ድምፃችን ይሰማ



ረቡእ ሚያዝያ 22/2006

በዶ/ር ሽፈራው እና በደህንነት መስሪያ ቤቱ አማካኝነት የሚመሩት የአዲስ አበባ እና የአማራ መጅሊስ አመራሮች መፈንቅለ ሥልጣን ዛሬ መፈጸማቸውን የቅርብ ምንጮች ገለጹ! ይኸው መፈንቅለ ስልጣን የፌዴራል መጅሊስና የአዲስ አበባ መጅሊስን ያመሰ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በዛሬው መፈንቅለ ስልጣን የፌዴራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸኽ ኪያር ሸኽ መሀመድ አማን፣ የፌዴራል መጅሊስ ዋና ጸሀፊ አቶ ሙሀመድ አሊ፣ ከአዲስ አበባ መጅሊስ ደግሞ ኢንጂነር ተማምና ሌላ አንድ ሀላፊ መነሳታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ከስልጣናቸው ተነሱ የተባሉት ፕሬዝደንቱ ሸኽ ኪያር በአሁኑ ሰአት ከአገር ውጪ በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በዛሬው መፈንቅለ ሥልጣን በሸኽ ኪያር ቦታ የኦሮሚያ ክልል ተወካዩ መተካታቸው ሲገለጽ፣ የአማራው ክልል ተወካይም የኡለማ ም/ቤቱን መረከባቸው ተሰምቷል፡፡

በዚህ ዛሬ ተጠናቀቀ በተባለው መፈንቅለ ስልጣን ታጋይ የነበሩት የትግራይ ተወካይና ም/ፕሬዝደንት ሸኽ ከድር፣ የአዲስ አበባው መጅሊስ ፕሬዝደንት ዶ/ር አህመድ እና የአማራ መጅሊስ ተወካይ አይነተኛ ሚና እንደነበራቸው የታወቀ ሲሆን ከኋላቸውም ዶ/ር ሽፈራውና የደህንነት ሀላፊዎች ሲመሩት ቆይቷል፡፡ የስልጣን ሽኩቻው ረዘም ላለ ጊዜ የቆየ ሲሆን በድሬዳዋ ከተማ በተካሄደው ጉባኤ ላይም ፈንድቶ እስከመውጣት ደርሶ ነበር፡፡ የሽኩቻው ዋነኛ ምክንያትም ከመንግስት በኩል በግዳጅ ህዝበ ሙስሊሙ ላይ ለመጫን ሲሞከር የነበረው የአህባሽ አስተሳሰብ ዳግም በህዝበ ሙስሊሙ ላይ መጫኑ እንዲቀጥል በሚፈልጉት ወገኖች እና ‹‹ህዝበ ሙስሊሙ ሲቃወመው የነበረው የግዳጅ ጠመቃ ቆሞ መጅሊሱ ሁሉንም ሙስሊም በአንድነት ሰብስቦ እና አቻችሎ መቀጠል አለበት›› በሚሉት ዛሬ ከስልጣን በተወገዱት ሀላፊዎች መካከል ያለው የአቋም ልዩነት መሆኑ ታውቋል፡፡

እስካሁን በነበረው ሂደት የመጅሊሱ ፕሬዝደንት ‹‹መጅሊሱ ህዝበ ሙስሊሙን የሚጠቅም እና በሰላም እንዲኖር የሚያደርግ እንጂ ችግር ውስጥ የሚያስገባ አካል መሆን የለበትም›› የሚል ፅኑ አቋም ይዘው የነበረ ሲሆን በሸኽ ከድር በሚመራው ቡድን እየተደረገ ያለውን ህዝበ ሙስሊሙን ዳግም ወደ ተቃውሞ ሊያስገባ የሚችል ትንኮሳ በመቃወምም ለተለያዩ የመንግስት አካላት ደብዳቤ መፃፋቸው ታውቋል፡፡

በሕገ ወጡ መጅሊስ ውስጥ ከላይ እስከታች የሚታየው የስልጣን ሽኩቻ የተቋሙን አመራር ሕገ ወጥነት አመላካች ከመሆኑም በላይ በመንግስት የተሰጠውን የቤት ስራ ለመፈጸም የተሰባሰበ ቡድን መሆኑንም ክስተቱ እማኝነት ሰጥቷል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎችና ማብራሪያዎች በነገው እለት ይኖሩናል - ኢንሻአላህ!

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!


በዋልድባ ገዳም እየተካሄደ ያለው እምነትን የማፍረስ ዘመቻ ዛሬም እንደቀጠለ በቦታው የሚገኙ መነኮሳት በምሬት ገለፁ፡፡


ድምጻችን ይሰማ ዘኦርቶዶክስ


ቀደም ሲል ወደ 20 የሚጠጉ ገዳማትን ለማፍረስ ተንቀሳቅሶ የነበረው የኢህአዴግ አፍራሽ ሀይል በመነኮሳት ፣ በባህታውያን፣… ፀሎትና በአካባቢው በሚገኙ ተቆርቋሪዎች ሲከሽፍበት የዘጉ ባህታውያንና ጨምሮ በርካቶችን በማሰር፣ በመደብደብ፣በማፈናቀልና በማንገላታት ጉዳት ማድረሱ ይታወቃል፡፡ በዚህም ያተረፈው 2ቱን ‹መሪዎችን› መለስ ዜናዊና ገ/ መድህን/ጳውሎስ ፣ በቦታው የሄዱ መሀንዲስና ሰራተኞችን፣ ጠበንጃ አንጋቾችን ጨምሮ በርካቶችን በሞት ሲነጠቅ በራሱ ላይ ከፍተኛ ችግር አድርሷል፡፡ ቃሌማ የተባለ የገዳሙ ዙሪያ በርካት ገበሬዎችን አፈናቅሎ ‹የስኳር› ተክል መዝራቱ ይታወቃል፡፡
ይሆንና በየጊዜው ኪሳራን እየተከናነበ በሀገርና በሕዝብ ላይ በደል የሚያደርሰው ኢህአዴግ በ16/ 08/ 2006 ዓ. ም በዕለተ ሀሙስ ማይ ለበጣ በተባለ ቦታ የገዳማትን ሰዎች ሰብስቦ፡-
1ኛ፡- ድልስ ቆቃ አቡነ- አረጋዊ ገዳም፣
2ኛ፡- መሀር ገፅ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም፣
3ኛ፡- እጣኖ ማርያም ገዳም ፣….‹ለስኳር ልማት› እንዲፈርሱ በቀጣይ ደግሞ ማይጋባ ቅ/ ጊዮርጊስ ‹ ይነሳሉ› የሚል ሀሳብ ሲያቀርብ በርካታ ተቃውሞ ቀርቦ ከፍተኛ ውዝግብ ፈጥሯል፡፡
በመህል የሰገሰጋቸው አሰሮች የድጋፍ ድምፅ ሲያሰሙ መነኮሳትና መናንያን ተቃውሞሙን በማጠናከራቸው ለግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ. ም ተቀጥሯል፡፡ በዚህም የዋልድባ ገዳም ተቆርቋሪ የሆናችሁ ሁሉ ድምፃችሁን አሰሙልን ሲሉ ተማፅነዋል፡፡


ለወይዘሮሪት ኢህአዴግዬ ሰው ማሰር ሻሽ ሸብ ከማድረግ እኩል ቀላል አይደለምን?! – አቤ ቶክቻዉ

ወዳጄ….
በሩቁ የምታውቀው ወዳጅህ ሲታሰር፤ አሳሪዎቹ የሚደረድሩልህ ምክንያት ትንሽ እውነት ሊኖረው ይችላል ብለህ ልታስብ ተችላለህ ከዛ አሳሪዎች መቼም ማሰር አይታክታቸውም አይደል፤ ቀረብ የሚልህ ወዳጅህን ደግሞ ያስራሉ፤ ማሰር ብቻም አይደል ያለ የሌላቸውን ምክንያቶች በቴሌቪዥን በራዲዮ አከታትለው ይነግሩሃል ይሄኔ ግራ ትጋባለህ …መንግስትን ያህል ነገር እንዲህ አይን አውጥቶ ሊዋሽ ይችላል….. ወይስ ወዳጄን በቀጡ አላውቀውም ነበር ብለህ ይምታታብሃል…
የኔ ጌታ አሳሪ ጠዋት ቀበቶውን ካሰረ ሰዓት አንስቶ ሙሉውን ቀን፤ “ደግሞ ማንን ልሰር….” ሲል ነው የሚወለው። እና እያለ፣ እያለ ከራስህ በላይ አውቀዋለው የምትለውን ወዳጅህን ወይም እራስህን ጥርቅም አድርጎ ያስራል። ይሄኔ የፈለግ ምክንያት ቢደረደርልህ አሳሪውን ልታምን እንደማትችል የታወቀ ነው ሀቁ ያለው ራስህ ጋ ነዋ!
እናም ወዳጄ…
በተለይ እንደ ኢህአዴግ ያለ የማሰር ሱስ ያለበት አሳሪ በሩቁ የምታውቃቸውንም በቅርብ የምታውቃቸውንም አስሮ ምክንያት ሲደረድር ወዳጆችህን አተጠራጠር እውነቴን ነው የምልህ መንግስታችን ሰዎችን ሲያስር ጥጃ የማሰር ያክል አይጨንቀውም። ለዚህ ደግሞ አጥጋቢ ምክንያት ሲፈልግ አየገኝም፤ በቃ የአይንህ ቀለም ካላማረው ያስርሃል።
የ ዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን የማውቃቸው ማንም ሰው የታሰረ እነደሆነ መዝገብ አገላብጠው መታሰሩ ከህግ አንጻር፣ ከህገ መንግስት አንጻር፣ ከሞራል አንጻር፤ እያሉ የህሊና ፍርድ ሲሰጡ ነው። ሙስሊም ሳይሉ ክርስቲያን ሳይሉ ኦሮሞ ሳይሉ ጋምቤላ ሳይሉ ያለ ለዩነት ጆሯቸው የደረስ አይናቸው ያየውን ኢፍትሃዊነት ሲያወግዙ ነው። ደግሞ ሲያውግዙ ብቻ አይምሰልህ መንግስት የሚሰራቸው መልካም ነገሮችም እውቅና ሊሰጠው ይገባል፤ ጽንፈኛ መሆን ተገቢ አይደልም ሲሉም ይውቅሱሃል።
ዛሬ መንግስት እነዚህን ወጣቶችን ሰባስቦ አስሯቸዋል። (ለወይዘሮሪት ኢህአዴግዬ ሰው ማሰር ሻሽ ሸብ ከማድረግ እኩል ቀላል ነው (በሌላ ቅንፍ ኢህአዴግዬን ወይዘሮሪት ያልኩታ ታግባ አታግባ በቀጡ ሰላላወቅሁ ነው፤ ግራ ስታገባን ግን በድንብ አውቃታለሁ… ሃሃ))
እኔ በአስሩም ጣቴ እፈርማለሁ፤ ዘጠኙም ጋዜጠኞች እና አስተያየት ሰጪዎች የታሰሩት እንደ ሰው በማሰባቸው እና በሀገራችን ጉዳይ ያገባናል በማለታቸው ብቻ ነው!
እንደዚህ የምልህ መንግስቴ ከሀገሬ አሯሩጦ ስላስወጣኝ ቂም ይዤ አለመሆኑን ድንጋይ ነክሼ እምልልሃለሁ!


የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ህግን ለማስከበር በመጣራቸው

 ተጨማሪ ቅጣት ተጣለባቸው!!



ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በቅስቀሳ ላይ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በ1000 (አንድ ሺህ ብር) ዋስ እንዲወጡ መወሰኑን ተከትሎ ‹‹እኛ ነጻ ነን፡፡ ገንዘብ አስይዘን እንወጣም፡፡ ስራችን ህግ ማስከበር እስከሆነ ድረስ እየታሰርንም ቢሆን ህግ እናስከብራለን፡፡ በመሆኑም ነጻ እስካልተለቀቅን ድረስ እሰሩን፡፡›› በማለታቸው ተጨማሪ ክሶችና ቅጣቶች እየተጣለባቸው ነው፡፡ 
በትናትናው ዕለት ሜሮን አለማየሁና ትግስት ወንዲፍራው ‹‹ግቢ በመረበሸ›› ተጨማሪ ክስ መከሰሳቸው ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ወቅት በቤላ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙ 14 ያህል የሰማያዊ ፓር አመራሮችና አባላትም ተመሳሳይ ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን ባለፈው ከፍላችሁ ውጡ ከተባሉት 1000 (አንድ ሺህ ብር) በተጨማ 600 (ስድስት መቶ ብር) ጨምረው ከፍለው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡
እነዚህ አመራሮችና አባላት መጀመሪያ የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የነበሩ ቢሆንም እስረኛውን በማሳመጽና በመረበሽ ከመከሰሳቸውም በተጨማሪ ወደ ቤላ ፖሊስ ጣቢያ ተዛውረዋል፡፡ በወቅቱ ድብደባና ማዋከብ እንደደረሰባቸው የሚናገሩት ታሳሪዎቹ ‹‹ህግን ለማስከበር የምናደርገውን ጥረት እንደ ህገ ወጥነት ተቆጥሮ ተጨማሪ ክስና በደል ቢፈጸምብንም እኛ ህግ ማስከበራችንን እንቅጥላለን›› ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ በጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙትና ዛሬ ስምንት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እያንዳንዳቸው 5500 ብር አስይዘው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ታሳሪዎቹ ይህንን ውሳኔ በመቃወም ‹‹ነጻ ካልተለቀቅን አንወጣም!›› ያሉ ሲሆን ከዳኛው የተሰጣቸው መልስ እንዳሳዘናቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ዳኛውና አቃቤ ህጉ ተመካክለው ነው የገቡት፡፡ በእያንዳንዳችን 5500 ብር እንድንከፍል ሲፈርዱ፤ ‹እኛ ተማሪዎችና የመንግስት ሰራተኞች ነን ከየትም አምጥተን መክፈል አንችልም!› አልናቸው፡፡ እነሱ ልክ አንድ ሰው እቃ ሲገዛ እንደሚከራከረው ‹በቃ! 2000 ብር ይሁንላችሁ› አሉን፡፡›› ያሉት ታሳሪዎቹ በህግ ሳይሆን በዘፈቀደ እየተሰራ መሆኑ አሳዝኗቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ‹‹ህገ ወጥ ቢሆንም በሌላ አካባቢ የታሰሩት የእኛ ጓደኞች 1000 ብር ነው እንዲከፍሉ የተወሰነባቸው፡፡ የእኛውን ለምንድን ነው 5500 ያደረጋችሁት?›› ብለው ሲጠይቁ ዳኛው ‹‹ቅጣቱ ከጣቢያ ጣቢያ ይለያያል፡፡›› የሚል አስገራሚ መልስ እንደሰጧቸው ገልፀዋል፡፡

Tuesday, April 29, 2014

''ድምፃችን ይሰማ'' አዲሱን የትግል ምዕራፍ አስመልክቶ ህዝበ ሙስሊሙ  የጋራ


 ግንዛቤ ይኖረው ዘንድ የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል::


ኢንተርኔት ተጠቃሚ ላልሆነው አብዛኛው የህብረተሰባችን ክፍል በወረቀት 

አባቶ በመስጠትና የድምፅ መልዕክቱን በማስደመጥ ኃላፊነታችንን እንወጣ!!!


ሙሉ  ፅሁፉን  ከዚህ  በፊት  ፖስት  ከተደረገው  ላይ ማግኘት  ይችላሉ  . . . . 

''ምድር ህላዌዋ ከተቦካበት ቅፅበት አንስቶ በለውጥ ምህዋር ላይ እየተሸከረከረች ትገኛለች፡፡ ቀኑ ሰዐቱን ጠብቆ ሲመሽ ብርሀን በጨለማ ይለዋጣል፡፡ ምሽቱ ተራውን ለቀን ሲያስረክብ ደግሞ ጨለማው በብርሃን ይለወጣል፡፡ ምድር ሁሌም በለውጥ ሀዲድ ላይ ትከንፋለች፡፡ ዛሬ ከትላንት፣ ነገም ከዛሬ ለውጥን ይቀባበላሉ፡፡ የሰው ልጅ የህይወት ዑደት ስለ ለውጥ ተፈጥሮዊነት አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡ ከአንቀልባ እስከ ከፈን በሚዘረጋው የህይወት ጅረት የሰው ልጅ ሲፈስ በበርካታ የለውጥ ድልድዮች ስር ያልፋል፡፡ . . . ''

መልእክት - ቁጥር  http://goo.gl/PtMfJt 


''ላለፉት ሁለት አመታት አንግበን የተነሳናቸው ሶስቱ የመብት ጥያቄዎች ምላሽ ያገኙ ዘንድ ደከመን ሰለቸን ሳንል በትዕግስት እየታገልን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ እነዚሁ ያሳለፍናቸው የትግል አመታት ሂደታቸው ፍፁም ያማረ ቢሆንም ሶስቱን ጥያቄዎች ማስመለስን ገደብ አድርገን የተጓዝናቸው የትግል ጎዳናዎች ግን የምንፈልገው ቦታ ሊያደርሱን አልቻሉም፡፡ መንግስትም ጉዳዩን አጢኖ እልባት እንዲያገኝ ከመትጋት ይልቅ በአጉል ስም ማጥፋት ተጠምዶ ትግሉን በሀይል ለማስቆም እየባተለ ይገኛል፡፡ሙስሊሙ ህብረተሰብ የሀይል እርምጃው ሳይገታው ‹‹ጥያቄዎቹ አለተመለሱም›› ሲል ትግሉን ቢቀጥልም የመንግስት አፀፋ ግን ለሞት እና ለጅምላ እስር ዳርጎታል፡፡ ቀን በቀን በተተካ ቁጥር የመንግስት እምቢተኝነትና የሚወሰደው እርምጃ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አልታየም፡፡ ይህም ሆኖ ግን ትግሉ ከተጀመረበት ቅፅበት አንስቶ ባሳለፋቸው ሂደቶች የተከፈሉት ከፍተኛ መስዕዋትነቶች በርካታ የድል ፍሬዎችንም አስገኝተዋል፡፡ . . . ''

መልእክት - ቁጥር 2  http://goo.gl/VZLYjv 

''የኢትዮጲያ ሙስሊም በእምነቱ ላይ የተቃጣውን የአስተሳሰብና የመብት ጥሰት ዘመቻ ለመመከት፣ አስተሳሰቡን በኢስላማዊ አስተሳሰብ ለማረቅ፣ የሕግ ጥሰቱ በህግ ማእቀፍ ዕልባት ያገኝ ዘንድ ስላማዊ ትግል ሲጀምር መሪዎችን ከመፍጠሩም በላይ የተመሪነትን ስርዓት ለሀገራችን ታሪክ አዲስ በሆነ መልኩ ማሳየትና ማስተዋወቅ ችሏል፡፡ ሕዝቡ የፈጠራቸውን መሪዎች ያለጥርጥር ተከትሏል፡፡ ትዕዛዛቸውን ያለ ፍርሀት ተግብሯል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ በባለቤትነት በሚመራው በዚሁ የመብት ማስከበር ስላማዊ ትግል ሂደት ውስጥ ልክ እንደማንኛውም ትግል ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፏል፡፡ በርካታ መስዕዋትነት ከፍሏል፤ እየከፈለም ይገኛል፡፡ እስከ ድል ጫፍ በተዘረጋው የትግል ድልድይ ሲያልፍ እስራት፣ ድበደባ፣ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ፣ ስም ማጥፋትና መገለል ደርሶበታል፡፡ እነዚህ የትግል ገፅታዎች ህዝበ ሙስሊሙ በትግሉ መባቻ ላይ ከነበረው ቁመና ከፍ ያለ ተነሳሽነትና ፅናት ላይ እንዲገኝ አስችለውታል፡፡ በዚህም የአስተሳሰብ እመርታና የባህሪ ለውጥ ከማምጣቱም ባሻገር በትግሉ ሂደትም ላይ ተገቢ የሆነ የለውጥ ፍላጎት አሳድሮበታል፡፡. . .''

መልእክት - ቁጥር 3  http://goo.gl/zqdaiz 

''በሃምሌ 2003 የአህባሽ ጠመቃ ዋነኛ መንስኤነት የተጀመረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የመብት ማስከበር ትግል ትላልቅ እርከኖችን አልፎ መጥቷል፡፡ አሁን ወደ ቀጣዩ እርከን የሚሸጋገርበት ወሳኝ ወቅት ላይ ይገኛል፡፡ እስካሁን በነበረው ሂደት ትግሉ ይዞት ከተነሳቸው ሶስት ጥያቄዎች አለመመለስ ውጭ እጅግ ውጤታማ ሂደት ነበር፡፡ ምናልባት ጥያቄዎቹ ቢመለሱ ሊሰጡት ከሚችሉት ጥቅም በላይ ሌሎች ትልልቅ ፋይዳዎችን ለኡማው አበርክቷል፡፡ ከውጤቶቹ አንዱ ደግሞ ህዝባችን መብታችንን ማስከበር እና ከውስጥ ጉዳያችን የመንግስትን ጣልቃ-ገብ እጆች ማስወጣት ጊዜ ሊሰጠው እንደማይገባ በይፋ መናገር የሚችልበት ደረጃ ላይ መድረሱ ነው፡፡. . . ''

መልእክት - ቁጥር 4  http://goo.gl/H2JjNn

TPLF/EPRDF charges nine bloggers and journalists with inciting violence!!




(Reuters) – Ethiopia has charged six bloggers and three journalists with attempting to incite violence, their supporters said on Monday, prompting accusations from rights groups that the government is cracking down on its critics.
All nine defendants, including freelance journalists Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, appeared in court on Sunday after they were rounded up by police on April 25 and April 26, their colleagues told Reuters.
On Monday, Human Rights Watch (HRW) called on U.S. Secretary of State John Kerry, who visits Ethiopia on Tuesday, to press the government to “unconditionally release” all the defendants, but Addis Ababa dismissed the criticism of the case.
“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, HRW’s deputy Africa director.
“The timing of the arrests – just days before the U.S. secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech,” she said in a statement.
In 2012, Addis Ababa sentenced a prominent blogger and five other exiled journalists to between eight years to life on charges of conspiring with rebels to topple the government.
In the new case, a colleague of Tesfalem said security officials in plain clothes searched his house and confiscated several materials before taking him to a detention center.
An Ethiopian government official defended the case against the nine, saying it had nothing to do with muzzling the media.
“CRIMINAL ACTIVITIES”
“These are not journalists. Their arrest has nothing to do with journalism but with serious criminal activities,” Getachew Reda, an adviser to Prime Minister Hailemariam Desalegn, said.
“We don’t crack down on journalism or freedom of speech. But if someone tries to use his or her profession to engage in criminal activities, then there is a distinction there,” Getachew told Reuters.
Critics say Ethiopia – sandwiched between volatile Somalia and Sudan – regularly uses security concerns as an excuse to stifle dissent and clamp down on media freedoms.
They also point to an anti-terrorism law, passed in 2009, which stipulates that anyone caught publishing information that could incite readers to commit acts of terrorism can be jailed for between 10 and 20 years.
Addis Ababa says the law aims to prevent “terrorist attacks” as it is fighting separatist rebel movements and armed groups.
A court in Addis Ababa adjourned the hearing for the group of bloggers and journalists until May 7 and 8.
Kerry will meet Prime Minister Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom in Addis Ababa to discuss peace efforts in the region and to strengthen ties with Ethiopia, State Department spokeswoman Jen Psaki said in a statement.
The State Department says the aim of Kerry’s African tour – which will also take in Democratic Republic of Congo and Angola – is to promote democracy and human rights.
(Editing by James Macharia and Gareth Jones)
April 29, 2014

Ethiopian Authorities lie about crackdown against Free Speech!!


AFP – Ethiopia said Tuesday several people had been arrested on charges of “serious criminal activities”, but rights groups identified those detained as journalists and bloggers targeted in a sweeping crackdown against free speech.
“They are suspected of some serious crimes, and the police are investigating,” government spokesman Getachew Reda told AFP, without providing details of the alleged crimes.
The journalists and a group of bloggers known as “Zone 9″ were arrested last week, prompting an outcry from rights groups.
The Committee to Protect Journalists (CPJ) called the arrests “one of the worst crackdowns against free expression” in the country, while Amnesty International said it was part of a “long trend of arrests and harassment of human rights defenders, activists, journalists and political opponents.”
Leslie Lefkow of Human Rights Watch said the “arrests signal, once again, that anyone who criticizes  the Ethiopian government will be silenced”, and called for their immediate release.
The arrests come ahead of a visit this week by US Secretary of State John Kerry.
“The timing of the arrests — just days before the US Secretary of State’s visit — speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech,” Lefkow added.
The bloggers Zone 9 website, reportedly named after the prison where political detainees are held, listed the names of nine people arrested, saying they were charged with having worked with foreign human rights activists to foment violence or instability.
But the government dismissed the rights groups, and said those arrested were not detained for their work as journalists.
“We don’t take orders from Human Rights Watch,” Getachew said. - Free speech ‘a crime’ -
An opposition group staged a protest on Sunday following the arrests, calling for “greater liberties and a true democracy” in Ethiopia, but police shut the 200-person demonstration down soon after it started.
HRW said 20 members of the political opposition Semayawi or “Blue” party have also been arrested since Friday, although there has been no official confirmation of exact numbers.
“With the latest arrests, Ethiopian authorities are turning the peaceful exercise of free expression into a crime,” the CPJ’s Tom Rhodes said in a statement.
Amnesty said the group had only restarted blogging last week after suspending their work for the past six months, accusing the government of harassment.
Ethiopia has been accused of cracking down on independent media and has doled out several heavy sentences for journalists charged under the controversial anti-terror legislation, which rights groups have called vague and far-reaching.
“With still a year to go before the general elections, the Ethiopian government is closing any remaining holes in its iron grip on freedom of speech, opinion and thought in the country,” said Amnesty’s Claire Beston.
In 2011, two Swedish journalists were sentenced to 11 years in jail under the law, but were later pardoned after serving 15 months.
Ethiopia has one of the most closed press environments in the world, the CPJ says. It calculates that at least 49 journalists have been forced into exile, the third worst after Somalia and Iran.
@Alula Zewge

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትግል መሪ የሆነው ''ድምፃችን ይሰማ'' የፌስቡክ ፔጅ

 ለአዲሱ የትግል ምዕራፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንቅስቃሴ ጀመረ!!!

''ድምፃችን ይሰማ'' አዲሱን የትግል ምዕራፍ አስመልክቶ ህዝበ ሙስሊሙ  የጋራ

 ግንዛቤ ይኖረው ዘንድ የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል::

መልዕክት ቁጥር 4 እነሆ! 

#EthioMuslimStruggle 
አዲሱን የትግል ምእራፍ አስመልክቶ የጋራ ግንዛቤ እንዲኖረን የተላለፈ መልእክት - ቁጥር 4

የቀጣዩ የትግል እርከን መነሾዎች!
ማክሰኞ ሚያዝያ 21/2006

በሃምሌ 2003 የአህባሽ ጠመቃ ዋነኛ መንስኤነት የተጀመረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የመብት ማስከበር ትግል ትላልቅ እርከኖችን አልፎ መጥቷል፡፡ አሁን ወደ ቀጣዩ እርከን የሚሸጋገርበት ወሳኝ ወቅት ላይ ይገኛል፡፡ እስካሁን በነበረው ሂደት ትግሉ ይዞት ከተነሳቸው ሶስት ጥያቄዎች አለመመለስ ውጭ እጅግ ውጤታማ ሂደት ነበር፡፡ ምናልባት ጥያቄዎቹ ቢመለሱ ሊሰጡት ከሚችሉት ጥቅም በላይ ሌሎች ትልልቅ ፋይዳዎችን ለኡማው አበርክቷል፡፡ ከውጤቶቹ አንዱ ደግሞ ህዝባችን መብታችንን ማስከበር እና ከውስጥ ጉዳያችን የመንግስትን ጣልቃ-ገብ እጆች ማስወጣት ጊዜ ሊሰጠው እንደማይገባ በይፋ መናገር የሚችልበት ደረጃ ላይ መድረሱ ነው፡፡

መንግስት ጥያቄዎቹን ላለመመለስ እየተከተለው ያለው አካሄድ ሙስሊሙ እንደዜጋ ከሚጋፈጣቸው ዘርፈ ብዙ ችግሮች በተጨማሪ እምነቱን ብቻ መሰረት ያደረገ ነጥሎ የማጥቃት ዘመቻውን በዕቅድ ይዞ እንደሚሰራው መላው ህዝብ በማያሻማ ሁኔታ መረዳቱ ለዚህ ደረጃ መደረስ ዋና ምክንያት ነው፡፡ የጥያቄዎቻችን ቀላል ይዘት፣ ያቀረባቸው መላው ሙስሊም ከመሆኑ እና ከሁለት አመታት በላይ በፅናት ከመዝለቁ ጋር ተዳምሮ መልስ ሊነፈግ የቻለው በአንድ እና አንድ ምክንያት ነው፡- ይኸውም ሃምሌ 2003 ይፋ የሆነው የመንግስት ዕቅድ የአጠቃላይ ዘመቻው አንዲት ማሳያ ብቻ በመሆኑ! ይህ ማሳያ ፊት ለፊት የሚታገል ህዝብ ባያጋጥመው የት ድረስ እንደሚጓዝ መገመት አይከብድም፡፡ በትግል ውስጥ ላለ አንድ ማህበረሰብ ደግሞ ይህንን መረዳት ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡

ሰላማዊ የመብት ትግላችን ሶስት ውስን ጥያቄዎችን አስቀድሞ ሲመርጥ ጥያቄዎቹ የሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ብቸኛ ሃገራዊ አጀንዳዎች ስለሆኑ አልነበረም፡፡ የህዝበ ሙስሊሙ የመታገል አቅም እና አካሄድ ‹‹አምባገነኖችን ተክቼ ፍትህን በየደረጃው ለማስፈን ቆሜያለሁ›› የሚልን መንግስት ሶስት ጥያቄዎችን እንዲመልስ ለማድረግ እንደማያንስ አስቀድሞም ይታወቅ ነበር፡፡ ጥያቄዎቹን ውስን ማድረግ ግድ የሆነው መንግስት ሃገር ለማስተዳደር፣ ህዝብ ደግሞ ሙሉ ዜግነት እንዲሰማው መሟላት ያለባቸው መሰረታዊ መብቶች ከአጠቃላይ የሃገሪቱ ማህበረ-ፖለቲካ ጉዞ ጋር እንደሚፈቱ በማመን ነበር፡፡ እነዚህ መሰረታዊ መብቶች አሁንም ከአጠቃላይ የሃገሪቱ ሂደት ጋር ተዳምረው የሚታዩ ቢሆንም ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ መብቶቹን ከሌላ አካል እንደሚበረከቱለት ገፀ በረከቶች አድርጎ የሚጠብቅበት እድልም ተስፋም አግባብም እንደሌለ የሁለት አመት ሰላማዊ ትግላችን ጥርት ባለ መልኩ አሳይቶናል፡፡

ዛሬ ላይ ባነሳቸው ውስን ጥያቄዎች ሽፋን እየተገፈፉ የመጡት ሌሎች መሰረታዊ መብቶች አካሄዳቸውን ለመቀልበስ የማይቻልበት ደረጃ ከመድረሱ በፊት ህዝበ ሙስሊሙ እውነታውን ሊረዳ፣ ተረድቶም ተግባራዊ እርምጃ ሊወስድ ግድ ይለዋል፡፡ የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄም ነው፡፡ ከሁለት አመታት በፊት ከህዝብ ከተሰበሰቡት በርካታ ጥያቄዎች ሶስት ሲመረጡ በወቅታዊነታቸው፣ በአንገብጋቢነታቸው መሆን ያለባቸው እና መሆን የሚችሉ እንደሆኑ በመታመኑ ነው፡፡ እነዚያ ጥያቄዎቻችን ዛሬም አንገብጋቢ እና መሆን ያለባቸው ናቸው፡፡ ነገር ግን እነሱ እውን እንዲሆኑ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ ማድረግ የወቅታችን ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ግድ ነው፡፡

ህዝብ ባስቀመጠው ሰፊ የእፎይታ ጊዜ ውስጥ ሰላማዊ ትግላችንን አስመልክቶ ጥልቅ ፍተሻ እና ቀጣይ ጉዞን በሚመለከት ህዝብ አሳታፊ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ የፍተሻው አበይት ውጤት የሚጠቁመው ያነሳናቸውን ሶስት ጥያቄዎች ለማስመለስ የአቅምም ሆነ የአካሄድ ጉድለት አለመኖሩን ነው፡፡ በተቃራኒው ያለማቋረጥ እየደረሱ ያሉት የመብት ጥሰቶች አንድ ህዝብ ሊያነሳቸው ከሚችላቸው የሰላማዊ ትግል አጀንዳዎች ትልቁን ለማንሳት የሚያስገድዱ ነበሩ፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ግን ዛሬም እንደከዚህ ቀደሙ ብሶት መርሁን እንዳይስት አላደረገውምና ለጥያቄዎቹ አለመመለስ ጥያቄዎቹ የቀረቡበትን አግባብ እና የቀረቡለትን አካል መፈተሽ እንደሚያስፈልግ የጋራ ስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ በነዚህ ህዝብ አሳታፊ ፍተሻዎች እና የቀጣይ ጉዞ የማስቀመጥ ስራ የትግል ጥያቄዎቻችን አንድ... ሁለት... ሶስት... እየተባሉ ተነቅሰው የሚወጡ፣ በጊዜ እና በቦታ የተገደቡ ውስን ነጥቦች አይደሉም፡፡ ይልቁንም አስፈላጊው ነገር የችግሮቻችንን ምንጭ ታሳቢ ያደረገና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የሚካሄድ ሁሉን አቀፍ ጉዞ መሆኑ ግልጽ ሆኗል፡፡

የሰላማዊ ትግላችንን ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ መነሻ የሆነው እውነታ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ባለፉት ሁለት አመታት የከፈለው መስዋእትነትና ያዳበረውን አንድነት፣ ጥንካሬ፣ ትእግስትና ታዛዥነት በመጠቀም የበለጠ ተጠቃሚና ዘላቂ ወደ ሆነ ትግል ማሸጋገር መቻሉ ሲሆን በዝርዝር ድግሞ እንደሚከተለው ሊቀመጥ ይችላል፡-

•ሙስሊሙ ማህበረሰብ እየከፈለው ያለውን መስዋእትነት የበለጠ ውጤት-ተኮር ለማድረግ የሚያስችሉ ዘርፈ-ብዙ ስልቶችን በመንደፍ ሃይማኖታዊ መብታችንን ለማስከበር፣

•ህብረተሰቡ የታገለለት ዓላማ አካሄድ ሰላማዊ፣ ነገር ግን የተሟላ እንዲሆን ለማድረግ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት፣

•እየተከፈለ ያለው መስዋዕትነት ሰፊና ዘርፈ-ብዙ ፍላጎቶችን ሊሸፍን በሚችል መልኩ እንዲሆን ለማመቻቸት፣

•ሁሉም የህብረተስብ ክፍል ትዕግስትና ጥንካሬ ተላብሶ እንደየዘርፉ የሚቻለውን እንዲያበረክት በር ለመክፈት፣

በእነዚህ መነሻዎች የሚቃኘውን የህዝበ ሙስሊሙን ቀጣይ ሰላማዊ ትግል አስመልክቶ ከፊታችን ባሉት ተከታታይ ሳምንታት ሰፊ ግንዛቤ የማስጨበጥ እና የህዝብን አመለካከት መልሶ ለህዝብ የማንፀባረቅ ሰፊ ስራ ይኖራል፡፡ በዚህ ስራ ላይ መረጃዎችን በማሰራጨት፣ ትንተናዎችን በመስራት፣ ብዥታዎችን በማጥራት እና ለተግባራዊነታቸው በሙሉ አቅም በመስራት ረገድ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርግ እና የጀመርነውን ሰላማዊ ትግል ከጫፍ ለማድረስ የማይተካ ሚናውን እንደሚወጣ ይጠበቃል!

የትግል አቅጣጫ ማስገንዘቢያ መልእክቱን የድምጽ ትረካ ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ፡-
http://goo.gl/H2JjNn

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!


የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትግል መሪ የሆነው ''ድምፃችን ይሰማ'' የፌስቡክ ፔጅ

 ለአዲሱ የትግል ምዕራፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንቅስቃሴ ጀመረ!!!

''ድምፃችን ይሰማ'' አዲሱን የትግል ምዕራፍ አስመልክቶ ህዝበ ሙስሊሙ  የጋራ

 ግንዛቤ ይኖረው ዘንድ የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል::

መልዕክት ቁጥር 3 እነሆ! 


#EthioMuslimStruggle
አዲሱን የትግል ምእራፍ አስመልክቶ የጋራ ግንዛቤ እንዲኖረን የተላለፈ መልእክት - ቁጥር 3

የህዝቡን የለውጥ ፍላጎት መረዳት ተገቢ ነው!
ሰኞ ሚያዝያ 20/2006

የኢትዮጲያ ሙስሊም በእምነቱ ላይ የተቃጣውን የአስተሳሰብና የመብት ጥሰት ዘመቻ ለመመከት፣ አስተሳሰቡን በኢስላማዊ አስተሳሰብ ለማረቅ፣ የሕግ ጥሰቱ በህግ ማእቀፍ ዕልባት ያገኝ ዘንድ ስላማዊ ትግል ሲጀምር መሪዎችን ከመፍጠሩም በላይ የተመሪነትን ስርዓት ለሀገራችን ታሪክ አዲስ በሆነ መልኩ ማሳየትና ማስተዋወቅ ችሏል፡፡ ሕዝቡ የፈጠራቸውን መሪዎች ያለጥርጥር ተከትሏል፡፡ ትዕዛዛቸውን ያለ ፍርሀት ተግብሯል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ በባለቤትነት በሚመራው በዚሁ የመብት ማስከበር ስላማዊ ትግል ሂደት ውስጥ ልክ እንደማንኛውም ትግል ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፏል፡፡ በርካታ መስዕዋትነት ከፍሏል፤ እየከፈለም ይገኛል፡፡ እስከ ድል ጫፍ በተዘረጋው የትግል ድልድይ ሲያልፍ እስራት፣ ድበደባ፣ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ፣ ስም ማጥፋትና መገለል ደርሶበታል፡፡ እነዚህ የትግል ገፅታዎች ህዝበ ሙስሊሙ በትግሉ መባቻ ላይ ከነበረው ቁመና ከፍ ያለ ተነሳሽነትና ፅናት ላይ እንዲገኝ አስችለውታል፡፡ በዚህም የአስተሳሰብ እመርታና የባህሪ ለውጥ ከማምጣቱም ባሻገር በትግሉ ሂደትም ላይ ተገቢ የሆነ የለውጥ ፍላጎት አሳድሮበታል፡፡

ሕዝቡ በጊዜ ሂደት ይፈታሉ በሚል እሳቤ በይደር ያቆያቸው ሌሎች ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊም ሆነ ተያያዥ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ስር እየሰደዱ ከመሆናቸውም ባሻገር በገደብ የተሰጡትን መሰረታዊ መብቶችም መልሶ የመንጠቅ ስራ እየተሰራበት ይገኛል፡፡ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ዛሬም ከማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ብሎም የአንድን ሀገር እውቀት በማምረት መፃኢ እድሏን ከሚወስነው የትምህርት መድረክ በስልት እየተገፉ ይገኛሉ፡፡ ይህም ሙስሊሙ እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ ሳይሆን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቱን በሚያረጋግጡ መርሆች ላይ የተመሰረተ ሰፊ ትግል እንዲያደርግ ገፊ ከመሆኑም በላይ በፅኑ ተነሳሽነት የተወለደው ይኸው ግለት የለውጥ ፍላጎቱን አገንፍሎታል፡፡ የችግሮቹ ብዛትና ያለንበት ሁኔታ ሚዛን አለመድፋቱ የትግል ተሀድሶን እንዲሻ አስገድዶታል፡፡

ህዝበ ሙስሊሙ በሶስቱ ጥያቄዎች ሳይገደብ የመንግስትን ሴራዎችና ቀጣይ ፈተናዎችን ግምት ውስጥ በሚያስገባ መልኩ ለዘላቂና ሁለንተናዊ መፍትሄ እንዲንቀሳቀስ የማንቃት ስራ ለመስራት የተፈጠረው የለውጥ ፍላጎት አጋዥ እንደሚሆን ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ይህንኑ በለውጥ ፍላጎት የተሞላ የህዝቡን ስሜት በመረዳት፣ የወቅቱን ተጨባጭ እና የማስፈፀም አቅም ከግምት ያስገባ፣ በትግሉ ሂደት የተፈጠረውን ህዝባዊ ተነሳሽነትና የአንድነት ስሜት እንደለም አፈር በመጠቀም ዘርፈ ብዙ ችግሮቹን ለመፍታት የሚችልበትን የተሀድሶ አቅጣጫ መንደፉ ተገቢ ሆኗል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ የትግሉ ባለቤት፣ የመሪዎቹም መሪ በመሆኑ ቀጣይ የትግሉን ሂደትና የተሀድሶ አድማስ የሚወሰነው የህዝበ ሙስሊሙን የልብ ትርታ፣ ስሜትና የለውጥ ፍላጎት በመንተራስ ነው፡፡ ሕዝቡ በአጠቃላይ ሂደቱ አንድ እርምጃ ወደፊት መጓዝ ይፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የራስ ተነሳሽነት፣ አርቆ አሳቢነትና ቁርጠኝነት ሁነኛ ግብአቶች ይሆናሉ፡፡ ራሳችንን ለተሻለ ድል ከፍ እናድርግ፡፡

የትግል አቅጣጫ ማስገንዘቢያ መልእክቱን የድምጽ ትረካ ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ፡-
http://goo.gl/zqdaiz

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

 

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትግል መሪ የሆነው ''ድምፃችን ይሰማ'' የፌስቡክ ፔጅ

 ለአዲሱ የትግል ምዕራፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንቅስቃሴ ጀመረ!!!

''ድምፃችን ይሰማ'' አዲሱን የትግል ምዕራፍ አስመልክቶ ህዝበ ሙስሊሙ  የጋራ

 ግንዛቤ ይኖረው ዘንድ የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል::

መልዕክት ቁጥር 2 እነሆ! 

#EthioMuslimStruggle 
አዲሱን የትግል ምእራፍ አስመልክቶ የጋራ ግንዛቤ እንዲኖረን የተላለፈ መልእክት - ቁጥር 2

የትግላችን ሂደት ለውጥ ግድ እንደሚል ማስረጃ ነው!
እሁድ ሚያዝያ 19/2006

ላለፉት ሁለት አመታት አንግበን የተነሳናቸው ሶስቱ የመብት ጥያቄዎች ምላሽ ያገኙ ዘንድ ደከመን ሰለቸን ሳንል በትዕግስት እየታገልን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ እነዚሁ ያሳለፍናቸው የትግል አመታት ሂደታቸው ፍፁም ያማረ ቢሆንም ሶስቱን ጥያቄዎች ማስመለስን ገደብ አድርገን የተጓዝናቸው የትግል ጎዳናዎች ግን የምንፈልገው ቦታ ሊያደርሱን አልቻሉም፡፡ መንግስትም ጉዳዩን አጢኖ እልባት እንዲያገኝ ከመትጋት ይልቅ በአጉል ስም ማጥፋት ተጠምዶ ትግሉን በሀይል ለማስቆም እየባተለ ይገኛል፡፡ሙስሊሙ ህብረተሰብ የሀይል እርምጃው ሳይገታው ‹‹ጥያቄዎቹ አለተመለሱም›› ሲል ትግሉን ቢቀጥልም የመንግስት አፀፋ ግን ለሞት እና ለጅምላ እስር ዳርጎታል፡፡ ቀን በቀን በተተካ ቁጥር የመንግስት እምቢተኝነትና የሚወሰደው እርምጃ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አልታየም፡፡ ይህም ሆኖ ግን ትግሉ ከተጀመረበት ቅፅበት አንስቶ ባሳለፋቸው ሂደቶች የተከፈሉት ከፍተኛ መስዕዋትነቶች በርካታ የድል ፍሬዎችንም አስገኝተዋል፡፡

የትግላችን ሂደት በመስዋዕትነትና በድል ፍሬዎች መሀል እየፈሰሰ ይገኛል፡፡ እነዚህ መስዕዋትነቶችም ሆነ ፍሬዎች የትግሉን አቅጣጫ የማስመርም ሆነ የማስቀየር እምቅ ሀይል ተሸክመዋል፡፡ በመንግስት እየተወሰዱ ያሉት የተጠኑ፣ አንዳንዴም የስማ በለው እርምጃዎች የጥንካሬን እንጂ የተስፋ መቁረጥን በር ሊከፍቱ አልቻሉም፡፡ የሀሰት ውንጀላው፣ ስም ማጥፋቱ፣ መስጂድ ነጠቃው፣ ጤናማ ኢስላማዊ እንቅስቃሴዎቹን ማፈኑ ፍርሀትን ሳይሆን ትግሉን ሊያጎለብቱ የሚችሉ ቁጭትና ጥንካሬዎችን ፈጥሯል፡፡ ከጀመዓ፣ ከብሄር፣ ከአካባቢ፣ እንዲሁም ከኑሮ ደረጃ የልዩነት ማዕቀፎች በመውጣት ለትግሉ ጉዞ ምቹ ከባቢን የሚፈጥር አንድነት በዙሪያችን ተፈጥሯል፡፡

ያለፉት ሁለት አመታት የትግላችን ሂደት መገለጫ የሆኑት መስዕዋትነትና የድል ፍሬዎቹ ያዳበሩት አንድነት፣ ጥንካሬ፣ ቁርጠኝነት፣ ትዕግስተኝነት እና ታዛዥነትን በመጠቀም ሙስሊሙ ህብረተሰብ እየከፈለ ያለውን መስዕዋትነት የበለጠ ውጤት ተኮር ወደሆነና ዘላቂነት ወዳለው የትግል ምዕራፍ ማሸጋገር እና የአቅጣጫ ለውጥ ማድረጉ አስፈላጊ እንደሆነ ታምኖበታል፡፡

የአቅጣጫ ለውጡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በገዛ ሀገሩ መብት ጠያቂ ያደረጉትን እንቅፋቶችን ጥሶ በማለፍ በሀገራችን ሁለንተናዊ እድገቶችና ለውጦች ላይ ንቁ ተሳትፊ እንዲሆን የአመለካከት ለውጥ በመፍጠር፣ የታገለለትን አላማ ሰላማዊ፣ ነገር ግን የተሟላ በማድረግ፣ እየተከፈለ ያለውን መስዕዋትነት ዘርፈ ብዙ ፍላጎቶችን ሊሸፍን በሚችል መልኩ በማዋል፣ እንዲሁም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ትዕግስትና ጥንካሬ ተላብሶ እንደየዘርፉ የሚቻለውን እንዲያበረክት የሚያስችል በር የሚከፍት እንዲሆን የትግላችን ሂደት ያስገድዳል!

የትግል አቅጣጫ ማስገንዘቢያ መልእክቱን የድምጽ ትረካ ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ፡-
http://goo.gl/VZLYjv

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትግል መሪ የሆነው ''ድምፃችን ይሰማ'' የፌስቡክ ፔጅ

 ለአዲሱ የትግል ምዕራፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንቅስቃሴ ጀመረ!!!

''ድምፃችን ይሰማ'' አዲሱን የትግል ምዕራፍ አስመልክቶ ህዝበ ሙስሊሙ  የጋራ

 ግንዛቤ ይኖረው ዘንድ የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል::

መልዕክት ቁጥር 1 እነሆ! 

አዲሱን የትግል ምእራፍ አስመልክቶ የጋራ ግንዛቤ እንዲኖረን የተላለፈ መልዕክት - ቁጥር 1

ለውጥ፤ ተፈጥሯዊ ሂደት!
ቅዳሜ ሚያዝያ 18 /2006

ምድር ህላዌዋ ከተቦካበት ቅፅበት አንስቶ በለውጥ ምህዋር ላይ እየተሸከረከረች ትገኛለች፡፡ ቀኑ ሰዐቱን ጠብቆ ሲመሽ ብርሀን በጨለማ ይለዋጣል፡፡ ምሽቱ ተራውን ለቀን ሲያስረክብ ደግሞ ጨለማው በብርሃን ይለወጣል፡፡ ምድር ሁሌም በለውጥ ሀዲድ ላይ ትከንፋለች፡፡ ዛሬ ከትላንት፣ ነገም ከዛሬ ለውጥን ይቀባበላሉ፡፡ የሰው ልጅ የህይወት ዑደት ስለ ለውጥ ተፈጥሮዊነት አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡ ከአንቀልባ እስከ ከፈን በሚዘረጋው የህይወት ጅረት የሰው ልጅ ሲፈስ በበርካታ የለውጥ ድልድዮች ስር ያልፋል፡፡ 

የታሪክ መዘውርን ስንቃኝም ይህንኑ አውነታ ነው የምናገኘው፡፡ ለዚያም ነው ነብያት ይዘወት የሚመጡት አስተምህሮ ይዘት ወጥ ቢሆንም አፈፃፀሙና ቅርፁ ግን የለውጥን ተፈጥሯዊነት ባገናዘበ መልኩ የተቃኘና ከየወቅታዊው ተጨባጭ ጋር እንዲገጥም የተለያየ የሆነው፡፡

የሰውን ልጅ የታሪክ ምዕራፍ ሰፊውን ቦታ የሚሸፍነው ትግል ነው፡፡ በተለያዩ ወቅቶች የሰው ልጆች በግልም ይሁን በህብረት ለተለያየ አላማና ግብ ትግሎችን አካሂደዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ትግሎች ጭቆናን ለማሰወገድ የተደረጉ ሲሆኑ መነሻና መድረሻቸው የተራራቀ ቢሆንም ሁሉም ለውጥ በተባለ ተፈጥሯዊ ምህዋር ላይ ግን አልፈዋል፡፡ የትግሎች መወለድ፣ የአድማሳቸው መስፋት፣ መጎልበት፣ ብሎም ወደ ስኬት መዳረሻ የሆኑ ጎዳናዎችን እንደተጨባጩ መቀያየር የተፈጥሯዊው ለውጥ አንድ አካል ነው፡፡ ያለ ለውጥ ውጥናቸውን ያሳኩ ትግሎች፣ የድል ደጃፍ የደረሱ እንቅስቃሴዎች በታሪክ ማህደራት ውስጥ አይገኙም፡፡

ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላለፉት ሁለት አመታት በእምነታችን ላይ የተቃጣውን ዕኩይ ተልዕኮ ለመመከት በትዕግስት፣ በፅናትና በቁርጠኝነት እየታገልን እንገኛለን፡፡ በዚህ የትግል ሂደት ከመባቻው ጀምሮ ነባራዊ ሁኔታውን ባማከለ መልኩ በተለያዩ ምዕራፎች ውስጥ አልፈናል፡፡ የመጀመሪያው የትግል ሂደት ውስንና ተጨባጩ በፈቀደው መልኩ በአንድ ቦታ በመሰባሰብና በመወያየት ጭምር የነበረ ሲሆን እርከኑን ጠብቆ በማደግ በአንድ ቅጥር ግቢ ከመወሰን ዘልሎ ሁሉንም ማዳረስ የቻለውም ተፈጥሯዊውን የለውጥ ዱካ ተከትሎ ነው፡፡ የመንግስትን መዋቅር ተከትሎ አቤቱታዎችን ከማስገባት ሂደቱ ጎን ለጎን ብቅ ያለው የመስጂድ ተቃውሞም የዚሁ የለውጥ ፍሬ ነው፡፡ ቅርፃቸው የተለያዩት የተቃውሞ ሂደቶችና መርሀ-ግብሮች ተለዋዋጩ ነባራዊ ሁኔታ የወለዳቸው ናቸው፡፡ ከኮሚቴዎቻችን በግፍ መታሰር ማግስትም ትግላችን የይዘት ሳይሆን የቅርፅ ለውጥ አምጥቷል፡፡ የትግሉ ባለቤት የሆነው ህዝበ ሙስሊሙ ንቃትና ብሰለት ከዕለት ወደ ዕለት ዕድገትና ለውጥ ማሳየት፣ ብሎም የሀገሪቱ እና አለም አቀፍ ተጨባጭ መቀያየር በተለያዩ ጊዜያት ትግሉ ለውጥ እንዲያመጣ የበኩላቸውን ተፅዕኖ አሳርፈዋል፡፡

ዛሬ ላይም ያነሳናቸውን ጥያቄዎች መንግስት ለመመለስ ፍቃደኛ አለመሆኑን መሰረት አድርጎ ሙስሊሙ ህብረተሰብ እየከፈለ ላለው መስዕዋትነት የሚመጥን ተገቢ የሆነ ሰፊ አጀንዳ ማስቀመጥ ተፈጥሯዊው የለውጥ ምህዋር የሚወልደው ተሀድሶ በመሆኑ በዚያው መስመር በአላህ ፈቃድ መፍሰሳችንን እንቀጥላለን!

የትግል አቅጣጫ ማስገንዘቢያ መልእክቱን የድምጽ ትረካ ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ፡-
http://goo.gl/PtMfJt

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!

አላሁ አክበር! 




The Charge Opened on Zone 9's and Journalists

"አገሪቷን በሶሻል ሚዲያ ለማተራመስ ራሱን የመብት ተሟጋች ነኝ ብሎ ከሚጠራ የውጭ ኃይል ጋር በሐሳብም በገንዘብም ተረዳድተውና ተስማምተው በአገሪቷ ላይ የብጥብጥ ቅስቀሳ ለማነሳሳት አቅደው ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል::"